Posts

የአለታ ወንዶ ወረዳ ሴቶች ለምርጫው መዘጋጀታቸውን ገለጹ

አዋሳ መጋቢት 09/2005 በመጪው ሚያዚያ ወር በሚካሄደው የዞን፣ የወረዳና ቀበሌ ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ መጋጀታቸውን በሲዳማ ዞን የአለታ ወንዶ ወረዳ ሴቶች ገለጹ፡፡ ከወረዳው ሴቶች መካከል አንዳንዶቹ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በምርጫው መብትና ጥቅማቸውን የሚያስከብርላቸውን ለመምረጥ ከወዲሁ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይ የወረዳው ሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጽሕፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ አዛለች ካያሞ እንዳስረዱት በአለታ ወንዶ 29 የገጠርና ከተማ ቀበሌዎች ለምርጫው ከተመዘገበው 59ሺህ ያህል ህዝብ ግማሽ ሴቶች ናቸው፡፡ በተመራጭ፣በአስመራጭና ታዛቢነት ከወንዶች እኩል ስብጥርና ተሳትፎ እንዳላቸው አስታውቀው በመራጭነትና በተመራጭነት የተመዘገቡት ሴቶች በስርዓቱ ያገኙትን ተጠቃሚነት ዘላቂ ለማድረግ ሰርተው የሚሰሩ ተወካዮቻቸውን ለመምረጥ እለቱን በጉጉት እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ በድርጅት ለወረዳ ምክር ቤት በዕጩነት ከቀረቡት መካከል ወይዘሮ አልማዝ ዲንጋሞ ቢመረጡ ሴቶች ከወንዶች እኩል ሆነው በማህበራዊ ፣ በኢኮኖሚና ፓለቲካ ያላቸውን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ጠንክረው ለመስራት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ በድርጅታቸው ተወክለው ለምርጫው ተሳታፊ በመሆናቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ በመራጭነት ከተመዘገቡት መካከል ወጣት አሰለፈች በቀለና እመቤት ተሰማ ሴቶች ለዘመናት ሲደረስባቸው ከነበረው የጾታ ተጽዕኖናና ጭቆና ተላቀው ባገኙት መብት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቀው በቀጣዩ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ጥቅሞቻቸውን የሚስጠብቁላቸውን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን አስረድተዋል፡፡

ደኢህዴን ያስገነባው አዳራሽና ማሰልጠኛ ማዕከል ተመረቀ

አዋሳ መጋቢት 09/2005 የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደኢህዴን/ ከ64 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ በጀት ያስገነባው ቢሮ ማስልጠኛ ማዕከልና የመሰብሰቢያ አዳራሽ ዛሬ ተመረቀ። ድርጅቱ ከአባላት መዋጮ ባሰባሰበው ገቢ የክልሉን ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ባህላዊና ፖለቲካዊ እሴቶችን በሚያንጸባርቅ ሁኔታ ያስገነባውን ቢሮ ማሰልጠኛ ማዕከልና የመሰበሰቢያ አዳራሽ መርቀው የከፈቱት የደኢህዴንና ኢህአዴግ ሊቀመንበር አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ናቸው። በ548 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የተገነባውና ለቢሮ አገልግሎት የሚውለው ባለሁለት ፎቅ ህንጻ 57 ለተለያየ አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎችና አራት የመሰብሰቢያ አዳራሾችን የያዘ ነው። የጉባኤ አዳራሹ በአንድ ሺህ 790 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈና በአንድ ጊዜ አንድ ሺህ 360 ሰዎችን የመያዝ አቅም ያለው ቁሳቁስ የተሟሉለትና ሶስት መለስተኛ የመወያያ ክፍሎች ፣የእንግዳ ማረፊያዎች ያሉት መሆኑ ተገልጿል። በአንድ ጊዜ ሁለት ሺህ 500 ሰልጣኞችን ተቀብሎ ማስተናገድ የሚችለው የስልጠና ማዕከል 30 የስልጠና ክፍሎች ፣10 የአስተዳደር ቢሮዎችና ሌሎች አገልግሎት መስጫ ክፍሎችን የያዘ በአንድ ሺህ 760 ካሬ ሜትር ቦታላይ ያረፈ መሆኑ ተገልጿል። http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=6432&K=1

Ethiopia’s Human Rights Crisis Worsened

By Betre Yacob. The human rights situation in Ethiopia, the most important strategic and security ally of the Western powers, has worsened drastically, according to the 2013 Human Rights Watch’s World Report, which summarizes the human rights situation of more than 90 countries worldwide—drawing on events from the end of 2011 through November 2012. The 665 page report says that Ethiopia’s dictatorial regime has deliberately continued to severely restrict fundamental rights of freedom of expression, association, and assembly. In addition, the report indicates that intimidation, arbitrary arrest, torture, forced displacement, and killing remain routine throughout the country. The report, which reflects extensive investigative work that Human Rights Watch undertook in collaboration with local human rights activists, was released in the beginning of February 2013. Providing heartbreaking examples, cases, and photographs, the report explains enough how dramatically the human rights

የደ.ኢ.ህ.ዴ.ን. 8ኛ ጉባዔ በሀዋሳ ተጀመረ

Image
የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደ.ኢ.ህ.ዴ.ን./ 8ኛ ጉባዔ መጋቢት 9/2005 ረፋድ ላይ በሀዋሳ ከተማ ተጀመረ፡፡ በጉባዔው መክፈቻ የድርጅቱ ሊቀመንበር ጠቅላይ ሚ/ር ኃይለማርያመ ደሳለኝ  ደ.ኢ.ህ.ዴ.ን. መስመሩን በማጥራትና ልማታዊ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብን በማጉላት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርግ ልማት እንድረጋገጥ አድርጓል ብለዋል፡፡ በደቡብ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ለተመዘገበው የኢኮኖሚ እድገት የክልሉ ህዝብ ከፍተኛ ሚና እንደነበረው አቶ ኃይለማርያም ገልፀዋል፡፡ የታላቁ መሪ መለስ ዜናዊን መስዋዕትነት ተከትሎ የክልሉ ህዝብ ራዕያቸውን ለማስቀጠል በገባው ቃል መሰረት የህዳሴ ጉዞውን ለማሳካት እየተካሄደ ያለው ጥረት የሚበረታታ ነው ብለዋል፡፡ በደቡብ ክልል የተጀመሩትን የልማት ስራዎች በማጠናከርና ለልማት ሰራዊት ግንባታ ትኩረት በመስጠት በተደራጀ መልኩ ሁለንተናዊ ዕድገት ለማስመዝገብ የድርጅቱ አባላትና ደጋፊዎች የአመራርነት ሚናቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርና የድርጅቱ ም/ሊቀመንበር አቶ ሽፈራው  ሽጉጤ  በበኩላቸው የታላቁ መሪ መለስ ዜናዊ ሁለንተናዊ የልማት ስራዎችን በእልህ ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ጥረት በሚደረግበት ወቅት ላይ ጉባዔው የሚካሄድ መሆኑን በመግልጽ በሰላም በድልና በልማት ጎዳና ሆነን  የሚካሄደውን ጉባዔ ውሳኔዎች የክልሉ ህዝብና መንግስት ለማስፈፀም ዝግጁ ናቸው ብለዋል ፡ ፡ በጉባዔው ላይ 1200 ታዳሚዎች  በመሳተፍ ላይ ሲሆኑ የተለያዩ ፓርቲዎች ለደ.ኢ.ህ.ዴ.ን. ያላቸውን አጋርነት በመግለፅ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ http://www.ertagov.com/amerta/component/content/article/48-erta-tv-today-top-

ከተፈሪ ኬላ ሀገረሰላም ጋታሜ ቦናን ጨምሮ በደቡብ ክልል ሶስት ዞኖች ከ42 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የመንገድ ግንባታ እየተካሄደ ነ

  ዲላ መጋቢት 08/2005 በክልሉ ሶስት ዞኖች ከ42 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የአዳዲስና ነባር መንገዶች ግንባታ በማከናወን ላይ መሆኑን የደቡብ ክልል መንገዶች ባለስልጣን የዲላ ዲስትሪክት ገለጸ። የትራንስፎርሜሽን እቅዱን በተሳካ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረገ በመንገድ ዘርፍ እየተካሄደ ያለው እንቅስቃሴ ጉልህ ድርሻ እንዳለው የጌዴኦ ዞን አስተዳዳሪ ገለጹ። በደቡብ ክልል መንገዶች ባለስልጣን የዲላ ዲስትሪክት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ዩሃንስ ዱከሌ ትናነት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ከያዝነው ዓመት ጀምሮ በጌዴኦ ሲዳማና ሰገን ህዝቦች ዞኖች 200 ኪሎሜትር አዲስና ከ500 ኪሎ ሜትር በላይ ከባድና ቀላል የመንገድ ጥገና ስራ እያከናወነ ይገኛል። ለመንገዱ ጥገና መንግስት 22 ሚሊዮን ብር ለአዲስ መንገድ ስራ ከ19 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት መመደቡን ገልጸው መንገዶቹ ወረዳዎችን ከዞን ከተሞችና ዞኖችን ከዞን የሚያገናኙ ደረጃቸውን በጠበቀ ሁኔታ የሚገነቡ መሆኑ አስታውቀዋል። አዲስ ከሚገነቡት መንገዶች መካከል በጌዴኦ ዞን ከገደብ ወርቃ ጎቲቲ 60 ኪሎ ሜትር ፣በሰገን ህዝቦች ዞን ከሶያማ ሰገን ከተማ ፣በሲዳማ ዞን ከተፈሪ ኬላ ሀገረሰላም ጋታሜ ቦና እንደሚገኝበት ገልጸዋል። የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበባየሁ ታደሰ በበኩላቸው መንግስት የትራንስፎርሜሽን እቅዱን ተግባራዊ ለማድረገ ከዘረጋቸው የልማት ስራዎች መካከል ዋነኛው መንገድ መሆኑን ተናግረዋል። ባለፈው አመት በተጀመረው የቀበሌ ተደራሽ መንገድ ከ116 ኪሎ ሜትር የሚበልጥ መንገድ መጠናቀቁን ገልጸው በመንግስት በጀት የተያዘላቸው የገደብና ይርጋጨፌ ኢዲዶ መንገድ ፕሮጀክቶች በክልሉ መንገዶች ባለስልጣን እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል። አርሶ አደሩ በተለይ የቡና ምርቱን በተቀላጠፈ ሁኔታ ለእንዱስትሪዎች