Posts

ኢትዮጵያ የቀርከሃ ዘላቂ ልማት መሰረት በመጣል አረንጓዴ ኢኮኖሚን ግንባታ ስትራቴጂ ቀይሳለች -ግብርና ሚኒስቴር

Image
ኢትዮጵያ የቀርከሃ ተክልን ዘላቂ ልማት መሰረት በመጣል አረንጓዴ ኢኮኖሚዊ  የግንባታ ስትራቴጂ መቀየሷንና የዘርፉን ኢንዱስትሪ የማስፋፋት ስራም አጠናክራ መቀጠሏን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ አህጉራዊ የቀርከሃ አውደ ጥናት መጋቢት 6/2005 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ሲጀመር የግብርና ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ምትኩ ካሳ እንዳስታወቁት በኢትዮጵያ ያለው የቀርከሃ ሃብት እንዲጠበቅና በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውል የሚያስችል ስትራቴጂ ተነድፎ ተግባራዊ እየተደረገ ነው፡፡ የቀርከሃ ልማት በአገሪቱ እንዲጠናከርና ከተክሉ የሚገኙ ልዩ ልዩ ውጤቶችንና ምርቶችን በማስፋፋት ጥቅም እንዲውሉ መንግስት የጀመረውን ጥረትና ቁርጠኝነት ደረጃ በደረጃ እያጠናከረ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ የዓለም ዓቀፉን የቀርከሃና ራታን ኔት ወርክ ለሁለት ዓመታት በሊቀ መንበርነት እንድትመራ በ15ኛው የተቋሙ የምስረታ ዓመት ላይ በቅርቡ መመረጧን አስታውሰው የተቋሙ ምክር ቤት በቻይና ባካሄደው 8ኛ ጉባኤ ይህን ኃላፊነት ለኢትዮጵያ መስጠቱንም ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም በአውሮፓውያን 2014 ዘጠነኛውን የኔትወርኩ ምክር ቤት ጉባዔን ኢትዮጵያ እንድታስተናግድ መመረጧን ገልጸው ጉባኤውን አዲስ አበባ ለማስተናገድ መዘጋጀቷንም አመልክተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከ15 ዝርያ የሚበልጡ የቀርከሃ ተክል ያለባት አገር መሆኗን አስታውሰው ይህን ተክል በማልማት የአካበቢ መጎሳቆልንና የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል አገራዊና አህጉራዊ ብቻ ሳይሆን ዓለም ዓቀፋዊ ሚናዋን ኢትዮጵያ እንደምትጫወት አስታውቀዋል፡፡ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ታደሰ ኃይሌ በበኩላቸው ቀርከሃ ለፋብሪካ ግብዓት ከሚውሉ የደን ውጤቶች አንዱ በመሆኑ ለኢንቨስትመንትና የስራ ዕድል በ

ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም፣ የአቶ መለስ ምትክ ወይስ የፕሬዝዳንት ግርማ?

አሁን በቀጥታ አንድ ጥቅስ ታነባላችሁ፤ የሀሳቦቹን ተጠየቂያዊ (Logical) ጥምረት ትታችሁና የአሁኑ ሀገር ተረካቢ ወጣት ላይ የተጣለውን ተስፋ በመልካም ጐኑ አድንቃችሁ ብቻ ይህን ጥቅስ አንብቡት፤ “የትላንት ፖለቲከኞች ዛሬም እንደ ትላንቱ በጥላቻ ፖለቲካ ላይ ተቸክለው በቀሩበት ወጣቶቻችን በሚዛናዊ ቅኝት ረጅም ርቀት መጓዝ መጀመራቸው ለአገራችን እጅግ በጣም ትልቅ ተስፋ ነው… ወጣቶቻችን የመለስን ምክሮች በውስጣቸው አስቀርተው የህይወት መመሪያቸው ማድረግ መጀመራቸውም መለስን እንዳላጡት ይልቁንም በእያንዳንዳቸው ታዳጊ ልቦና ውስጥ ትንሽ ቦታ እንደሠጡት፣ እርሱንም መሆን እንደጀመሩ የሚያመላክት ነው፡፡ እናም መለስ በሰማኒያ ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን ተተክቷል ስንል ከእውነታ ብዙም ያልራቅንበት ምክንያት መለስን በወጣቶቻችን ሚዛናዊ አስተሳሰብ ወስጥ ማግኘት በመጀመራችን ጭምር ነው፡፡” (ገፅ 33፣ አፅንኦቱ የእኔ ነው)፡፡ ከዚህ በላይ የቀረበውን ጥቅስ ሃሳብ፣ ምንጩን ከመጥቀሴ በፊት ደግማችሁ አንብቡትና ከወቅቱ የተለያዩ ሀገራዊ ክስተቶች ጋር አናቡት - በቃ፡፡ ለሀገሩ መልካም የሚመኝ ሁሉ፣ በሀገር ተረካቢው ትውልድ ላይ የተጣለው ተስፋ በራሱ፣ ልቡን በሀሴት ሞቅ የሚያደርገው ይመስለኛል፡፡ የሀገሩን እጣ ፈንታ በወጉ እየመረመረና እየመዘነ የፖለቲካ ሥርዓቱን መስመር በማሲያዝ የሚታትር ተተኪ ትውልድ የሌላትን ሀገር፣ ማንም ጤነኛ ዜጋ አይፈልጋትም፤ ተስፋ በተጣለባቸው ወጣቶች መደሰትም፣ ከዚሁ የሀገርን እጣ ፈንታ በእውቀት ከመወሰን አጠይቆት የመጣ ነው፡፡ አሁን ከላይ ወደ አነበባችሁት ጥቅስ ልመልሳችሁ። ጥቅሱ የተወሰደው፣ ኢህአዴግ የንድፈ ሃሳብ ማስተጋቢያዬ ናት ከሚላት “አዲስ ራዕይ” መፅሔት፣ ከጥቅምት 2005 ዓ.ም ልዩ እትም ነው፡፡ ልዩ እትም መፅሔቷ፤ “ለዋ

ኢትዮጵያን ጨምሮ 25 ገናና መንግስታት ተቃዋሚዎችን በኢንተርኔት ያጠምዳሉ ተባለ

በኢንተርኔት አማካኝነት የተቃዋሚዎችን መረጃ ለመሰለልና እንቅስቃሴያቸውን ለመከታተል የሚያገለግል ማጥመጃ ሶፍትዌር (Trojan horse) የሚጠቀሙ 25 አገራት እንዳሉ የገለፀ አንድ የካናዳ የጥናት ተቋም፤ ኢትዮጵያን በማካተት የበርካታ አገራትን በስም ጠቅሷል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት አስተባብሏል፡፡ ማጥመጃው ሶፍትዌር በተለያዩ መንገዶች የቫይረስ መከላከያ ዘዴዎችን አልፎ እየሾለከ ወደ ኮምፒዩተር መግባት የሚችል ሲሆን፤ መረጃዎችን ለመምጠጥ፣ ፓስዎርዶችን ለመስረቅ፣ የስልክና የስካይፒ ግንኙነቶችን ለመቅረጽ፣ በተለይም የኢሜይል መልእክቶችን ለመሰለል ያገለግላል ተብሏል፡፡ በቶሮንቶ ዩኒቨርስቲ “ስር ሲቲዘን ላብ” የተሰኘው የጥናት ተቋም ረቡዕ እለት ይፋ ባደረገው ማስጠንቀቂያ፤ ሰዎች በኮምፒዩተርና በሞባይል ስልክ ውስጥ የሚያስቀምጡት መረጃ እንዲሁም የሚለዋወጡት መልእክት ለስለላ የተጋለጠ ነው ብሏል፡፡ እንዲያውም በኮምፒዩተራችሁ ላይ የተገጠሙ ማይክሮፎኖችና ካሜራዎችን በመጠቀም ቤት ውስጥ የምታደርጉት እንቅስቃሴና የምትናገሩት ነገር ሁሉ፣ የስለላ አይንና ጆሮ ውስጥ ሊገባ ይችላል ብሏል፡፡ ለስለላ ያገለግላል የተባለውና “ፊንፊሸር” የተሰኘው ማጥመጃ ሶፍትዌር በተገኘባቸው አገራት ሁሉ፣ መንግስታት በተቃዋሚዎችና በዜጐች ላይ ስለላ ያካሂዳሉ ማለት ባይቻልም፤ እንደ ኢትዮጵያ የመሳሰሉ ገናና (authoritarian) መንግስታት እጅ ውስጥ መግባቱ ግን አሳሳቢ ነው ብሏል ተቋሙ፡፡ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የኢንፎርሜሽንና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በበኩላቸው፤ ስለማጥመጃ ሶፍትዌሩ የምናውቀው ነገር የለም ብለዋል፡፡ http://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&a

Hawassa constructing 184 mln. Birr worth safe water project

Image
Hawassa March 14/2013 More than 184 million Birr worth safe water project is being carried out in Hawassa Town, South Ethiopia Peoples' State, the town administration water and sewerage department said Department Head, Letta Yetamo told ENA that upon going fully operational within a year, the project will benefit more than 450,000 residents. He said the budget for construction of the project is secured from the regional government, the town administration, international donor organizations and NGOs. Safe water service coverage will grow to 100 per cent from the present 76 per cent when the project goes operational. http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=6315&K=0

ደኢህዴን በአለታ ወንዶ ወረዳ ከ5ሺ800 በላይ ዕጩዎችን ለዉድድር አቀረበ

Image
ሃዋሳ መጋቢት 6/2005 የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያ ንቅናቄ/ደኢህዴን/ በመጪው ሚያዚያ ለሚካሄደው የከተሞችና የአካባቢ ምርጫ በአለታ ወንዶ ወረዳ ከ5ሺህ 800 በላይ ዕጩዎችን ለዉድድር ማቅረቡን አስታወቀ ። በወረዳው የንቅናቄዉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ሀላፊ አቶ ከበደ ቱሚቻ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በምርጫው ንቅናቄውን ወክለው ለመወዳደር ከተዘጋጁት መካከል ግማሽ ያህሉ ሴቶች ናቸዉ ። ንቅናቄዉ እጩ ተወዳደሪዎችን ለምርጫ ያቀረበዉ በህዝብ ካስገመገምና ብቁነታቸዉን በይሁንታ ካረጋገጠ በኋላ መሆኑን አስታዉቀዋል ። ድርጅቱ ካዘጋጃቸው ዕጩ ተወዳዳሪዎች መካከል አምስቱ ለዞን ምክር ቤት፣ 87 ለወረዳ ምክር ቤቶች ቀሪዎቹ ደግሞ ለቀበሌ ምክር ቤቶች የሚወዳደሩ መሆናቸዉን ገልጠዋል ። ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊ ግልጽና በህዝብ ዘንድ አመኔታ አግኝቶ እንዲጠናቀቅ በንቅናቄው ደረጃ ሰፊ ጥረት ሲደረግ መቆየቱን አቶ ከበደ ጠቁመው በቀጣይነትም ሀዝቡ በመብቱ ተጠቅሞ የመሰለውንና ይበጀኛል የሚለዉን እንዲመርጥ አሳስበዋል ። ንቅናቄዉ ከተቃዋሚ ድርጅቶች ጋር የጋራ ምክር ቤት አቋቁሞ እየሰራ መሆኑን አመልከተው እስካሁን በምርጫው ለመሳተፍ የሚንቀሳቀስው የሲዳማ አርነት ንቅናቄ/ሲአን/ ቢሆንም በምርጫው ከማይሳተፈው ከኢትዮጵያዊያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ኢዴፓ/ ጭምር በጋራ ምክር ቤቱ አብረዉ እየሰሩ መሆናቸዉን ገልጠዋል ። በሌላ በኩል ደግሞ በወረዳው ለሚካሄደው ለዚሁ ምርጫ 58ሺህ 854 ህዝብ ተመዝግቦ ለመራጭነት የሚበቃውን ካርድ መውሰዱን የወረዳው ምርጫ ጽህፈት ቤት አስተባበሪ አቶ ወርቁ አኔቦ አመልከተዋል፡፡ ለመራጭነት ከተመዘገበው ህዝብ ውስጥ ከ27 ሺህ የሚበልጡት ሴቶች መሆናቸውን ጠቁመው በዕጩ ተወዳደሪነትም ከደቡብ ኢትዮጵያ ህ