Posts

የፖለቲካ ፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ ነገ የጀምራል

አዲስ አበባ ፣መጋቢት 3፣2005 (ኤፍ ቢ ሲ) ከአንድ ወር በኋላ በሚካሄደው ምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የተመደበላቸውን የአየር ሰዓትና የጋዜጣ አምድ በአግባቡ ሊጠቀሙበት እንደሚገባ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ አሳሰበ። በቀጣዩ ወር በመላ ሃገሪቱ ለሚካሄደው የአካባቢ ምርጫ ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ፥ የምረጡኝ ቅስቀሳ ዘመቻ በይፋ ከጀመሩ ትናንት 1 ወር መድፈናቸውን የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ ያመለክታል። ምንም እንኳን በዚህ ጊዜ ውስጥ ፓርቲዎቹ የተለያዩ መንገዶችን በመጠቀም ፕሮግራምና እቅዶቻቸውን ለህዝብ ማስተዋወቅ የሚችሉ ቢሆንም ፥ ባለፉት ሳምንታት ያነጋገርናቸው አብዛኞቹ ፓርቲዎች ግን ምንም ዓይነት የምረጡኝ ቅስቀሳ አለማድረጋቸውን ተናግረዋል። ፓርቲዎቹና በተለያዩ መንገዶች የሚያደርጓቸው የምረጡኝ ቅስቀሳዎች እንደተጠበቁ ሆነው ለአንድ ወር የሚቆየው እና በመገናኛ ብዙሃን የሚያደርጉት ቅስቀሳ ነገ ይጀምራል። ከብሮድካስት ባለስልጣን የተገኘ መረጃ እንደሚያመለክተው ፥ ከዚህ ቀደም በነበሩ ልምዶች ገዥውን ፓርቲ ጨምሮ የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙሃን የሚመደብላቸውን የአየር ሰዓትም ሆነ የጋዜጣ አምድ አሟጦ ያለመጠቀም ችግር አለባቸው። ለአብነት ያህል እንኳን በ2002ቱ ምርጫ 23 ያህል ፓርቲዎች ከተመደበላቸው ውስጥ ግማሹን ሳይጠቀሙበት ሲቀሩ ፥ 10 ፓርቲዎች ደግሞ በኤሌክትሮኒክስም ሆነ በህትመት መገናኛ ብዙሃን የተመደበላቸውን የጋዜጣ አምድና የአየር ሰዓት ሙሉ ለሙሉ አልተጠቀሙበትም። በመሆኑም በፓርቲዎቹ በኩል ይህ ሁኔታ ሊታረም እንደሚገባው ነው የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ነጋ ዱፊሳ የሚናገሩት። ሃላፊው ፓርቲዎቹ መገናኛ ብዙሃኑን ተጠቅመው መልዕክታቸውን በሚያስተላልፉበት ወቅት የምር

አነጋጋሪው የኢትዮጳያ የሰብአዊ መብቶች መርሃ ግብር

Image
አቶ እንዳልካቸው የኢትዮጵያ ህገ መንግሥት ሰብአዊ መብትን ከ 23 ባላነሱ አንቀፆች አካቶ መያዙን አስታውሰው በተግባር ግን በተዘዋዋሪ መንገድ በህገ መንግሥት የተጠቀሱትን መብቶች የሚዳፈሩ ና የሚሸረሽሩ ሌሎች ህጎች መውጣታቸውን ይዘረዝራሉ ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች መርኀ ግብር አስፈላጊ ቢሆንም ተግባራዊ ይሆናል ብለው እንደማይጠብቁ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ በምህፃሩ ሰመጉ ሃላፊና የአንድ ተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባል አስታወቁ ። የሰመጉ ሃላፊ ና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ የአመራር አባል ለዶቼቬለ በሰጡት አስተያየት ከልምድ እንደተገነዘቡት ኢትዮጵያ ውስጥ ችግሩ ህግ ማውጣት ሳይሆን በህገ መንግሥቱ የተደነገጉት ሰብአዊ መብቶች ተግባራዊ አለመሆናቸውና ይህንንም ተከታተሎ ማስፈፀም አለመቻሉ መሆኑን ተናግረዋል ። በተለያየ ደረጃ ውይይት የተካሄደበት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች መርሃ ግብር በቅርቡ የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲያፀድቀው ይቀርብለታል ተብሎ ይጠበቃል ። ሰነዱም ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት ቀርቦ ውይይት እንደተደረገበትና በሚኒስትሮች ምክርቤት ደረጃም እንደፀደቀ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት አስታውቀዋል ። ምንም እንኳን መንግሥት ፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸውን አካላት በመርሃ ግብሩ ላይ ማወያየቱን ቢገልፅም የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ በምህፃሩ ሰመጉ ግን ለውይይት አለመጠራቱንና የተባለው ሰነድም እንዳልደረሰው የሰመጉ ሃላፊ አቶ እንዳልካቸው ሞላ ለዶቼቬለ ተናግረዋል ።የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ የሥራ አስፈፃሚ አባልና የትምህርት ክፍል ሃላፊ አቶ ጌታቸው ባያፈርስ ድርጅታቸው የመርሃግብሩን ሂደት በመከታተል ላይ መሆኑን ለዶቼቬለ ተናግረዋል ። አቶ ጌታቸው ሌላው ቢቀር ሰመጉ ቢቻ

የኮንዶምኒዬም ልዩ ኮታ ለመንግስት ሰራተኞች! ልዩ ኮታው… ለፓርቲ አባላት መሆኑ ነው?

Image
ቢሆንስ ምን ችግር አለው? “ህዝብ” ናቸዋ! ችግር ቢኖረውስ የት ይደረሳል? ዝም ነው! ብዙዎቻችን ፈቅደን ያስጀመርነው አይደል! የመንግስት ሰራተኞች ከሌላው ዜጋ የበለጠ የኮንዶምኒዬም ኮታ እንደሚመደብላቸው ባለፈው ቅዳሜ እለት ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ሲናገሩ በጣም ነበር የገረመኝ። የመንግስት ሰራተኞች ከሌላው ዜጋ በምን ይበልጣሉ? በርካታ የፓርቲ አባላትን ስላሉበት ነው ልዩ እንክብካቤ የሚደረግላቸው? አይን ያወጣ አድልዎ መስሎ ስለሚታየኝ ነው የተገረምኩት፤ የደነገጥኩት። ረጋ ብዬ ሳስበው ግን፤ ለካ ያን ያህልም አስገራሚ አይደለም። “ኧረ ጉድ!” የሚል ሰውም አላጋጠመኝም። ደግሞም አዲስ የተፈጠረ ነገር የለም። የመንግስት ችሮታ፣ ከጥንት ጀምሮ የሚታወቅ የአገራችን ባህል ነው።  የድሮ ነገስታት፣ በነሱ ፊት ከሌላው ሰው በልጦ ለታያቸው “አገልጋይ”፣ ልዩ ድጋፍ ያደርጉ ነበር። “አገር ያቀና”፣ “በታማኝነት ያገለገለ”፣ “በትውልድ ሃረጉ የከበረ”፣ “በእምነቱ የፀና” … በሚሉ የተለያዩ ሰበቦች መሬት ይሰጡታል፤ መተዳደሪያ ገቢ የሚያገኝበት ግዛት ይሸልሙታል። እንደፈቃዳቸውም፣ ላሰኛቸውና ስሜታቸውን ለነካው ሰው ወይም ተወዳጅነትን ያስገኛል ብለው ሲያስቡ ለመንገደኛ ሁሉ ምፅዋት ለመስጠት እጃቸውን ይዘረጋሉ። አልያም፣ “ስጠው” ብለው የግምጃ ቤት ተቆጣጣሪውን ያዝዙታል። አልያማ ንጉስነታቸውና መንግስትነታቸው ምኑ ላይ ነው?  በእርግጥ ነገሥታት መሬት ጠፍጥፈው አይሰሩም። ማሳ አርሰውና ብረት ቀጥቅጠው መተዳደሪያ ገቢ አያመርቱም። ግን ችግር የለውም። ያው፤ ከአንዱ ዜጋ መሬት ነጥቀው ለሌላው ይሰጣሉ። ዜጎችን እያስገበረ መተዳደሪያ ገቢ እንዲያገኝ፣ ከወንዙ ማዶና ከተራራው ወዲህ ያለውን ግዛት ሰጥቼሃለሁ ይሉታል። ትንሽ ቆንጥረው ለተወሰኑ ዜጎች በምፅዋት ያከፋፍላሉ። “ለተ

ተቃዋሚዎች የአየር ሰአት ድልድሉ ፍትሃዊ አይደለም አሉ

Image
የአካባቢና ማሟያ ምርጫ ተወዳዳሪ ፓርቲዎች ራሳቸውን ለመራጩ ህዝብ እንዲያስተዋውቁ በሚል በምርጫ ቦርድ እና በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የተደለደለው የቴሌቪዥንና የሚዲያ የአየር ሰአት ፍትሃዊ አለመሆኑን ፓርቲዎች ገለፁ፡፡ የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ (ኢራፓ)፣ የኢትዮጵያ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ሃይሎች ግንባር (ኢፌዲሃግ) እና የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) አመራሮች እንደሚሉት፤ ለኢህአዴግ የተሰጠው የቴሌቪዥን የአየር ሰአት በአጠቃላይ 210 ደቂቃ ሲሆን ለእያንዳንዱ ተቃዋሚ ፓርቲ በኢቲቪ 1 እና ኢቲቪ 2 በእያንዳንዳቸው 10 ደቂቃ ብቻ የተሰጠ ሲሆን ይሄም ገዥው ፓርቲ በተቆጣጠረው ሚዲያ ሰፊ የአየር ሽፋን ማግኘቱን እንደሚያመለክት ገልፀዋል፡፡ የአየር ሰአት ድልድሉ በተለይ ፓርቲዎቹ የሚያቀርቧቸው እጩዎች ብዛት እና በ2002 ዓ.ም በተደረገው ምርጫ ፓርቲዎቹ ባገኙት የፓርላማ ወንበር መሆኑ የድልድሉን ፍትሃዊ አለመሆን ያጐላዋል ያሉት አመራሮቹ፤ እነዚህን መስፈርቶች ብቻ መመዘኛ ከማድረግ ይልቅ ሌሎች የዲሞክራሲ ሂደቱን ሊደግፉ የሚያስችሉ አማራጭ መስፈርቶችም ሊካተቱበት ይገባ ነበር ብለዋል፡፡ ፓርቲያቸው የአየር ሰአት ድልድሉ ፍትሃዊ ነው ብሎ ባያምንም ላለመግባባት መግባባት የሚለውን መርህ በማንገብ አብሮ በሰላምና በመግባባት መስራት የፓርቲያቸው ተቀዳሚ አላማ በመሆኑ እንደተቀበሉት የተናገሩት የኢራፓ ሊ/መንበር አቶ ተሻለ ሰብሮ፤ ለእያንዳንዱ ፓርቲ 10 ደቂቃ ብቻ በቴሌቪዥን መሰጠቱ፣ በተቃራኒው ለኢህአዴግ 210 ደቂቃ መመደቡና የ2002 ምርጫ ውጤትንና የእጩ ብዛትን እንደመስፈርት መውሰዱ የአየር ሰዓት ድልድሉ ፍትሃዊ አለመሆኑን ይጠቁማል ብለዋል፡፡ ኢዴፓ ሊቀመንበር አቶ ሙሼ ሰሙ በበኩላቸው፤ ለድልድሉ የቀረበው ደቂቃ ለፓርቲያቸው ምንም ጥ

በሃዋሳ ከተማ ከቱሪስቶች ከ39 ሚሊዮን ብር የሚበልጥ ገቢ ተገኘ

Image
አዋሳ የካቲት 30/06/2005 በሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ስድስት ወራት የቱሪስት መስብህ ስፍራዎችን ከጎበኙ የሀገር ውስጥና የውጪ ቱሪስቶች ከ39 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የአስተዳደሩ ባህል፣ ቱሪዝምና መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ገለጸ፡፡ የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሮ ምህረት ገነነ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ገቢው የተገኘው በከተማው የሚገኙ ባህላዊ፣ የተፈጥሮና ታሪካዊ የመስብህ ሰፍራዎችን ከጎበኙ 103 ሺህ 408 እንግዶች ነው። የተገኘው ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ከሰባት ሚሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ጠቁመው ከቱሪስቶቹ መካከል 20ሺህ 612 የውጪ አገር ቱሪስቶች ናቸው ብለዋል፡፡ የቱሪስት ፊሰቱና ከቱሪዝም ዘርፍ የተገኘው ገቢ የጨመረው በሀገር ውስጥና በውጭ የከተማውን መልካም ገፅታ የሚያሳዩ የባህል ፌስተቫሎችና ልውውጦች ፣የማስታወቅያና ፕሮሞሽን ስራ በመሰራቱ እንዲሁም የቱሪስት አገልግሎት ተቋማትን ለማጠናከር በርካታ ስራ በመሰራቱ ነው ብለዋል፡፡ የቱሪዝም መረጃዎችን በመጠቀም የማስተዋወቅ፣ ለአስጎብኝዎች ስልጠና መስጠት፣ አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎችን በጥናት ተለይቶ ለጎብኝዎች ክፍት ማድረግና የከተማውን የቱሪዝም አቅም የተሟላ መረጃ መስጠት የሚችል "ቱሪዝም ፖቴንሻል ኦፍ ሃዋሳ ሲቲ" በሚል የተዘጋጀ መፅሔት በመሰራጨቱ ገቢው ለጨምር መቻሉን ተናግረዋል፡፡