የኬንያ ምርጫ ወዲህ የኢትዮጵያ ወዲያ
የኬንያ ምርጫ ወዲህ የኢትዮጵያ ወዲያ шаблоны RocketTheme Форум вебмастеров ኬንያ በአፍሪካ በተለይ ደግሞ በምሥራቅ አፍሪካ የተሻለ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ብቻ ሳይሆን የተረጋጋ ፖለቲካ ያላት ተብላ የምትደነቅ አገር ነበረች፡፡ እ.ኤ.አ በ2007 የተካሄደውን አገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ የተከሰተው የእርስ በእርስ ግጭት ግን ከአንድ ሺሕ በላይ ሰዎችን ለሕልፈት ሲዳርግ፣ ከ600 ሺሕ የሚበልጡ ከቀዬአቸው እንዲፈናቀሉ ምክንያት ሆኗል፡፡ ባለፈው ሰኞ የተከናወነው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ አጠቃላይ ሒደቱ ሰላማዊ የሚባል ቢሆንም፣ ከወዲሁ የሚያስፈራ ፍንጭ አሳይቷል፡፡ ምርጫው በአብዛኛው ሰላማዊ የሚሰኝ ቢሆንም፣ በወደብ ከተማዋ ሞምባሳ አካባቢ ሞምባሳ ሪፐብሊካን ምክር ቤት (MRC) በመባል የሚታወቅ ተገንጣይ ቡድን በቀሰቀሰው ግጭት ምክንያት የ19 ሰዎች ሕይወት ሊያልፍ ችሏል፡፡ ያለፈው ምርጫ የፈጠረው ጦስ ለኬንያውያን ያስፈራቸው መሆኑን በርካታ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች እየዘገቡ ሲሆን፣ ምርጫው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በታገዘ የድምፅ አሰጣጥ ዘዴ ተከናውኗል፡፡ የብዙዎቹ ሥጋት በዋና ተፎካካሪዎቹ መሀል ጎሳን መሠረት ባደረጉ የፖለቲካ ድጋፍና ድምፅ የማግኛ ሥልቶች ምክንያት፣ የምርጫ ውጤቱን አሜን ብሎ የሚቀበል ተፎካካሪ አይኖርም የሚል ነው፡፡ ይህ በድጋሚ ወደ ጎሳ ግጭት ሊመራል ይችላል በሚል፡፡ ኬንያና ኢትዮጵያ ወዴት? ኢኮኖሚዋ በምሥራቅ አፍሪካ የተሻለ አቅም እንዳለው የምትታወቀው ኬንያ ፊታውራሪ በሆነችበት የምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ (EAC) ኡጋንዳና ታንዛኒያን አስከትላ በአካባቢው በአንድ ፓስፖርት፣ በአንድ ዓይነት ገንዘብና በአንድ የተማከለ ሕገ መንግሥት የሚመራ የፖለቲካ ማኅበረሰብም ለመፍጠር ተስፋ ተጥሎባት ነበር፡፡ እንዳተባ