Posts

የሃዋሳ ከተማ አሰተዳደር ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ፡፡

Image
አዋሳ የካቲት 27/2005 የሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ስድስት ወራት ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የከተማው አስተዳደር ከንቲባ አስታወቁ ። የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ191 ሚሊዮን ብር በላይ ብልጫ አለው፡፡ ከንቲባው አቶ ዮናስ ዮሰፍ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ገቢዉ የተሰበሰበዉ ቀጥታና ቀጥታ ካልሆኑ ታክሶች፣ከማዘጋጃ ቤት አገልግሎትና ከሌሎች ገቢዎች ነዉ ። በከተማው የገቢ አስተዳደር ስራዎችን ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ የታክስ ማሻሻያዎችን ተግባራዊ በመደረጉ የተሰበሰበው ገቢ ካለፉት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ መሻሻል አሳይቷል ። ገቢዉ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ191 ሚሊዮን 252 ሺህ 029 ብር ብልጫ እንዳለው አስታዉቀዋል ። በከተማ አስተዳደሩ ተቀርፆ እየተተገበረ ያለው የታክስ ማሻሻያ ፕሮግራም፣ አዳዲስ ግብር ከፋዮች ወደ ታክስ ስርዓቱ መግባታቸውና ግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ግዴታውን በአግባቡ መወጣት መጀመሩ ለገቢው ማደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ጠቁመዋል። በግማሽ በጀት ዓመቱ የግብር ከፋዩን ቁጥር ለማሳደግ አመራሩ፣ ባለሙያውና ሌሎች የባለድርሻ አካላት ባደረጉት የተቀናጀ ጥረት በደረጃ ሀ እና ለ 1ሺህ 564 ግብር ከፋዮች ወደ ግብር ስርዓቱ መግባታቸውን የገለጹት አቶ ዮናስ እነዚህ ግብር ከፋዮች ግዴታቸውን በአግባቡ መወጣት ጀምረዋል ብለዋል ። በተጨማሪ በከተማ አስተዳደሩ የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽን መጠቀም ያለባቸው ግብር ከፋዮች መሳሪያውን ገዝተው እንዲጠቀሙና የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱ ጤናማና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን 1ሺህ 177 የሽያጭ መመዝገቢያ ማሽኖችን ለግብር ከፋዩ ህብረተሰብ እንዲሸጥ መደረጉን ገልጠዋል ። በቀጣ

መገናኛ ብዙሃን የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያደርጉትን የቅስቀሳ ፕሮግራም በተገቢው መንገድ ሊያስተናግዱ ይገባል

አዲስ አበባ የካቲት 27/2005 መገናኛ ብዙሃን በ2005 ዓ.ም ለሚካሄደው የአካባቢና የአዲስ አበባ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያደርጉትን የቅስቀሳ ፕሮግራም በተገቢው መንገድ እንዲያስተናግዱ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን አሳሰበ፡፡ ተወዳዳሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከመጪው መጋቢት 4 ቀን እስከ ሚያዚያ 4/2005 ድረስ ለሚያቀርቡት የምርጫ ቅስቀሳ የሬዲዮና የቴሌቪዥን የአየር ሠዓትና የጋዜጣ አምድ ድልድል በዕጣ ተከናውኗል፡፡ የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ልዑል ገብሩ በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት መገናኛ ብዙሃን ፓርቲዎች የሚያቀርቡትን የቅስቀሳ ፕሮግራም ህግና መመሪያው በሚፈቅደው መሰረት በአግባቡ ማስተናገድ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ድልድሉ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ባፀደቀው መመሪያ መሰረት መከናወኑንና 50 በመቶ ሁሉም ፓርቲዎች በእኩል የሚካፈሉት ሆኖ 30 በመቶ በሕዝብ ተወካዮችና በክልል ምክር ቤቶች ባላቸው ብልጫ፣ 20 በመቶውን ጊዜ ደግሞ ባቀረቡት እጩ ተወዳዳሪ ብዛት የሚጠቀሙ ይሆናል፡፡ በዚሁ መሰረትም 24ቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሬዲዮ 19 ሠዓት ከ20 ደቂቃ፣ በቴሌቪዥን 12 ሠዓትና በተለያዩ ጋዜጦች 48 አምዶችን ያለምንም ክፍያ የምርጫ ቅስቀሳቸውን እዲያካሂዱ መደልደሉን ተናግረዋል፡፡ ለዚሁ ስራ የተመደበው የአየር ሠዓትና የጋዜጣ አምድ በገንዘብ ሲተመን ዘጠኝ ሚሊዮን ብር ያህል መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ይህም ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ፖሊሲያቸውን፣ ስትራቴጂያቸውንና ፕሮግራማቸውን ለህብረተሰቡ በነጻነት እንዲያቀርቡ መንግሥት ካለው ቁርጠኝነት አንጻር የተደረገ ነው ብለዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በተደረጉ ምርጫዎች ልምድ እንደታየው የተመደበላቸውን የአየር ሠዓትና የጋዜጣ አምድ ያለመጠቀም ችግር መታየቱን ያስታወሱት አቶ ልዑል ፓርቲዎች የተሰጣቸውን እ

ሲዳማ ኔትን ጨምሮ 16 የኣሽከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋማት እገዳ ተጣለባቸው

Image
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 26፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ክልል ትራንስፖርት ቢሮ 16  የአሸከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋማት ላይ እገዳ ጣለ። በደቡብ ክልል ፍቃድ አግኝተው ስልጠና የሚያካሂዱ 36 የአሽከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋማትን ፥ በክልሉ የሚከሰተውን የትራፊክ አደጋ ለመከላከል ሲባል የክልሉ ትራንስፖርት ቢሮ  ተቋማቱን  በአመታዊ እቅዱ ያሳትፋቸዋል። የቢሮው ሃላፊ አቶ ታገሰ ኤሮሞ እንደሚሉት ፥ እንዲሳተፉ በተደረገበት እቅድ ደግሞ አንድ የአሽከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋም ለማሰልጠን ሊያሟላ የሚገባቸው መስፈርቶች ተካተዋል። የክልሉ ትራንስፖርት ቢሮ ባለሙያዎች በተቋማቱ ላይ ባደረጉት ግምገማ ፥ 8 ያህሉ በተገኘባቸው ጉድለት በማስጠንቀቂያ ሲታለፉ ፥ 16ቱ ደግሞ ስልጠናውን  የሚሰጡበት ተገቢ ቦታ  የሌላቸው ፣ የራሳቸው የማለማመጃ  መኪና ሳይኖራቸው በኪራይ የሚጠቀሙ  ፤ በቂ ክህሎት ያለው አሰልጣኝ ሳይኖራቸው በመስራታቸው እርምጃው ሊወሰድባቸው እንደተቻለ ይናገራሉ። 12 ተቋማት ደግሞ በተካደው ግምገማ አንጻራዊ ለውጥ በማምጣታቸው ያለምንም ማስጠንቀቂያ ስራቸውን እንዲቀጥሉ የተደረጉ ናቸው። በቤንች ማጂ ፣ ስልጤ ዞን ወራቤ ፣ ጋሞ ጎፋ ፣ ሲዳማ ፣ ደቡብ ኦሞ እና ጉራጌ ዞኖች ላይ የሚገኙ  ናቸው እነዚህ ተቋማት። ሲዳማኔት ፣ ፊውቸር ላይት ፣ ዎስመካ  ፣ ጋላክሲ ፣ መካነ ኢየሱስ ፣ መገናኛ ፣ ወራቤኬሪ ፣ ፍሬም ፣ ኢሻ ፣ ዱዛ ፣ ጂፎር ፣ ወገሹር ፣ አግነት ፣ እና ሚቴማ እርምጃው የተወሰደባቸው ተቋማት ናቸው። ተቋማቱ በስልጠና ላይ የሚገኙ ተማሪዎችን በተጓደለ መልኩ እንዳያስመርቁም  ፤ በየጊዜው ልዩ ክትትል እየተደረገባቸው ስልጠናውን እንዲጨርሱ  አቅጣጫ መቀመጡን ነው ሃላፊው የተናገሩት። እገዳ ስለተጣለባቸው ተቋማት ህብረተሰቡ እንዲያውቅ

በደቡብ ክልል ትምህርት ቤቶች መካከል ሲካሄድ የቆየው የስፖርት ውድድር በሲዳማ ዞን ትምህርት ቤቶች የበላይነት ተጠናቀቀ፡፡

Image
በውድድሩ በክልሉ 11 ዞኖች፣ ሶስት ልዩ ወረዳና በሃዋሳ ከተማ የሚገኙ ከ250 የሚበልጡ የሁለተኛና መሰናዶ ትምህርት ቤቶች የተወጣጡ ከ3ሺህ በላይ ወንድና ሴት ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ በውድድሩ የሲዳማ ዞን ትምህርት ቤቶች በጤረጴዛ ኳስ፣ በአትለቲክስ ወንዶችና ሴቶች በአጠቃላይ ውጤት አሸናፊ በመሆን ሰባት ዋንጫዎችን ወስደዋል፡፡ የካምባታ ጣምባሮ ዞን ትምህርት ቤቶች ደግሞ በእጅ ኳስ ወንዶችና ሴቶች፣ መረብ ኳስ ሴቶች ሶስት ዋንጫ በማንሳት ዞኑ ውድድሩን በሁለተኛነት እንዲያጠናቅቅ አስችሎታል፡፡ የጉራጌ ዞን ትምህርት ቤቶች ቅርጫት ኳስ በሁለቱም ፆታ አሸናፊ በመሆን ዞኑ በሶስተኛ ደረጃ ውድድሩን እንዲያጠናቅቅ ያደረጉት ሲሆን የሰገን አከባቢ ህዝቦች ዞን ትምህርት ቤቶች በእግር ኳስ፣የወላይታ ዞን በወንዶች መረብ ኳስ አሸናፊ በመሆን አንዳንድ ዋንጫ ወስደዋል፡፡ የሀዲያ ዞን ትምህርት ቤቶች ከመጀመሪያው እስከ   ፍፃሜው ባሳዩት ስፖርታዊ ጨዋነት የፀባይ ዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ ከየካቲት 10 እስከ 21/ 2005 በተካሄደው ውድድር ክልሉን ወክለው በአዲስ አበባ በሚካሄደው አገር አቀፍ የትምህርት ቤቶች ውድድር የሚሳተፉ ከ400 በላይ ስፖርተኞች ተመርጠዋል፡፡ የሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዮናስ ዮሴፍ ለውድድሩ አሸናፊዎች፣ ለኮከብ ዳኞች፣ ተማሪዎች፣ለውድድሩ መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማት፣ ድርጅቶችና ግለሰቦች ዋንጫ፣ ሜዳሊያና ምስክርወረቀት ካበረከቱ በኃላ እንደገለጹት ስፖርት ለአንድ አገር ማህበራዊና ኢኮኖሚ እድገት ከሚኖረው ፋይዳ በተጨማሪ በብሄር ብሄርሰቦች መካከል ያለውን አንድነትና የባህል ትስስር ለማጠናከር የላቀ ሚና አለው፡፡ መንግስት ይኸንን በመገንዘብ ከሁሉም የባለ

The Surprising PROCESS of Sidama Cuisine

Image
After 5 years of documenting the Sidama tribe’s food ways, Donna Sillan, MPH has completed the first “Sidama Cookbook” ever written to capture the traditional art of this ancient and unique cuisine.  It is an anthropological document to preserve the dying art of enset, the staple of the Sidama.  She spent time planting, processing and preparing enset in Ethiopia before attempted to capture what has only been transmitted orally to date and is on the verge of extinction. A blurb from Donna on her shocking process :  Sidama food takes the prize for being the most complicated, intricate, ancient food processed on the planet.   What strikes me as most amazing is the fact that an ancient people discovered “enset” and found out how to make it edible and determine its utility as a staple.  How did they figure it out hundreds of years ago? I wrote this book for two reasons. First of all, I admit, I’m obsessed with food and particularly exotic, ethnic food.   It is no wond