Posts

በደቡብ ክልል ትምህርት ቤቶች መካከል ሲካሄድ የቆየው የስፖርት ውድድር በሲዳማ ዞን ትምህርት ቤቶች የበላይነት ተጠናቀቀ፡፡

Image
በውድድሩ በክልሉ 11 ዞኖች፣ ሶስት ልዩ ወረዳና በሃዋሳ ከተማ የሚገኙ ከ250 የሚበልጡ የሁለተኛና መሰናዶ ትምህርት ቤቶች የተወጣጡ ከ3ሺህ በላይ ወንድና ሴት ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ በውድድሩ የሲዳማ ዞን ትምህርት ቤቶች በጤረጴዛ ኳስ፣ በአትለቲክስ ወንዶችና ሴቶች በአጠቃላይ ውጤት አሸናፊ በመሆን ሰባት ዋንጫዎችን ወስደዋል፡፡ የካምባታ ጣምባሮ ዞን ትምህርት ቤቶች ደግሞ በእጅ ኳስ ወንዶችና ሴቶች፣ መረብ ኳስ ሴቶች ሶስት ዋንጫ በማንሳት ዞኑ ውድድሩን በሁለተኛነት እንዲያጠናቅቅ አስችሎታል፡፡ የጉራጌ ዞን ትምህርት ቤቶች ቅርጫት ኳስ በሁለቱም ፆታ አሸናፊ በመሆን ዞኑ በሶስተኛ ደረጃ ውድድሩን እንዲያጠናቅቅ ያደረጉት ሲሆን የሰገን አከባቢ ህዝቦች ዞን ትምህርት ቤቶች በእግር ኳስ፣የወላይታ ዞን በወንዶች መረብ ኳስ አሸናፊ በመሆን አንዳንድ ዋንጫ ወስደዋል፡፡ የሀዲያ ዞን ትምህርት ቤቶች ከመጀመሪያው እስከ   ፍፃሜው ባሳዩት ስፖርታዊ ጨዋነት የፀባይ ዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ ከየካቲት 10 እስከ 21/ 2005 በተካሄደው ውድድር ክልሉን ወክለው በአዲስ አበባ በሚካሄደው አገር አቀፍ የትምህርት ቤቶች ውድድር የሚሳተፉ ከ400 በላይ ስፖርተኞች ተመርጠዋል፡፡ የሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዮናስ ዮሴፍ ለውድድሩ አሸናፊዎች፣ ለኮከብ ዳኞች፣ ተማሪዎች፣ለውድድሩ መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማት፣ ድርጅቶችና ግለሰቦች ዋንጫ፣ ሜዳሊያና ምስክርወረቀት ካበረከቱ በኃላ እንደገለጹት ስፖርት ለአንድ አገር ማህበራዊና ኢኮኖሚ እድገት ከሚኖረው ፋይዳ በተጨማሪ በብሄር ብሄርሰቦች መካከል ያለውን አንድነትና የባህል ትስስር ለማጠናከር የላቀ ሚና አለው፡፡ መንግስት ይኸንን በመገንዘብ ከሁሉም የባለ

The Surprising PROCESS of Sidama Cuisine

Image
After 5 years of documenting the Sidama tribe’s food ways, Donna Sillan, MPH has completed the first “Sidama Cookbook” ever written to capture the traditional art of this ancient and unique cuisine.  It is an anthropological document to preserve the dying art of enset, the staple of the Sidama.  She spent time planting, processing and preparing enset in Ethiopia before attempted to capture what has only been transmitted orally to date and is on the verge of extinction. A blurb from Donna on her shocking process :  Sidama food takes the prize for being the most complicated, intricate, ancient food processed on the planet.   What strikes me as most amazing is the fact that an ancient people discovered “enset” and found out how to make it edible and determine its utility as a staple.  How did they figure it out hundreds of years ago? I wrote this book for two reasons. First of all, I admit, I’m obsessed with food and particularly exotic, ethnic food.   It is no wond

Critic's Notebook: Third Wave cafés take coffee to new heights

Image
Pourquoi Pas coffee shop owners Tony Tanchaleune, left, and Tyler Mastantuono. The café is one of Montreal’s growing number of Third Wave coffee shops. Photograph by: Allen McInnis , The Gazette The name of the café was Pourquoi Pas Espresso Bar, and so briefly did I plan to visit that I double-parked my car on top of an Amherst St. slush bank. I was only going in to buy some coffee. Or so I thought … I nodded to the two hipster baristas working the counter and admired the mason jars filled with coffee, trying to decide whether this week’s beans would be from Honduras, Ethopia, Kenya, El Salvador or Guatemala. I flipped the tags on the coffee jars and noticed the producer, roasting procedure and altitude at which the coffee was grown were listed alongside the specific code for the variety and the roasting date. We’re miles from a can of Maxwell House here. No doubt about it, Pourquoi Pas is one of the city’s growing number of Third Wave coffe

የሚያዝያው ምርጫ ነጠላ አልበም - Quick Fix!

የመብራት ኀይል “ትራንስፎርመር” ተቃጠለ (ትራንስፎርሜሽኑስ?) ቴሌኮም “ሲምካርድ ከእኔ፤ ኔትዎርክ ከእናንተ” ቢለን ይሻላል ምርጫ ቦርድ “ምርጫው እንጂ ምህዳሩ አያገባኝም” ብሏል ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ የሞባይሌ ቴክስት ሜሴጅ (SMS) ድምፅ ነው፡፡ በጣም ተናደድኩኝ፡፡ ሰዓቱ እኮ ገና አንድ ሰዓት አልሆነም፡፡ ቀን ቀን በኔትዎርክ መጨናነቅ ከአገልግሎት ክልል ውጭ የሚሆነው ሞባይሌ በዚህ ሌሊት እንዴት ይረብሸኛል? ይሄኔ እኮ የራሱ የቴሌኮም ማስታወቂያ ይሆናል… ብዬ አሰብኩ፡፡ “የ100 ብር ካርድ ስትሞሉ 15 ደቂቃ ነፃ የአየር ሰዓት ታገኛላችሁ” የሚለው አይነት ማለቴ ነው (ፅድቁ ቀርቶብኝ በቅጡ በኮነነኝ!) ሌላ ሌላው ማትጊያ ቀርቶብን ኔትዎርክ ብናገኝ እኮ ይበቃን ነበር፡፡ አሊያም ደግሞ ሃቁን በይፋ ቢነግረን ቁርጣችንን እናውቀዋለን፡፡ “አያችሁ ከዛሬ ጀምሮ የኔትዎርክ ጉዳይ አይመለከተኝም፤ ሲም ካርድ ከእኔ፤ ኔትዎርክ ከናንተ” ቢለን እኮ አርፈን እንቀመጣለን፡፡ ወይም ኔትዎርክ ከቻይና እናፈላልጋለን ፡፡ ባለፈው ሳምንት በኢቴቪ በቀረበ የፓናል ውይይት ላይ የመብራት ሃይል ኮርፖሬሽንና የቴሌኮም ተወካዮች ከነዋሪዎች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችና ቅሬታዎች አጥጋቢ መልስ አጥተው ሲጨናነቁ አይቼ አፈርኩም አዘንኩም፡፡ አንድ አስተያየት ሰጪ ምን አሉ መሰላችሁ? “ለምን አልቻልንም ፤ ከአቅማችን በላይ ነው ብላችሁ እውነቱን አትነግሩንም? ስንት ዘመን ነው ይሄንን እየሰራን ነው… ያንን እያደረግን ነው የምትሉት!” ሲሉ አፋጠጧቸው፡፡ በነገራችሁ ላይ እቺ አባባል ለእነ ቴሌኮም ብቻ ሳይሆን ለእነኢህአዴግም ትሰራለች፡፡ አዎ አንዳንዴ እኮ ማመን አለባቸው (ስንት ዘመን በሽወዳ!) እናላችሁ --- እነኢህአዴግና ሌሎችም ሲያቅታቸው “አልቻልንም! ከአቅማችን በላይ ነው” ቢሉን ትልቅ ው

በሚቀጥለው ሳምንት የኢሕአዴግ አባል ፓርቲዎች ስብሰባ ይጀምራሉ

አራቱ የኢሕአዴግ መሥራች ፓርቲዎች ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ የየራሳቸውን ጠቅላላ ጉባዔ ይጠራሉ፡፡ በተናጠል የሚጠሩት የፓርቲዎቹ ጠቅላላ ጉባዔዎች ቀጣዮቹን የማዕከላዊ ምክር ቤት አባላት ይመርጣሉ፡፡ በእነዚህ ጉባዔዎች የሚመረጡት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ደግሞ ብሔራዊ ፓርቲያቸውን ወክለው ለኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የሚሆኑ ሰዎችን ይመርጣሉ፡፡ ብአዴን፣ ደኢሕዴግ፣ ኦሕዴድና ሕወሓት ጠቅላላ ጉባዔያቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ከመጋቢት 14 እስከ 17 ቀን 2005 ዓ.ም. በሚካሄደው የእናት ፓርቲያቸው (ኢሕአዴግ) ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ባህር ዳር ከተማ ይከታሉ፡፡  በዚህ የኢሕአዴግ ዘጠነኛ ጉባዔ ላይ ትኩረት ከሚያገኙ አጀንዳዎች መካከል የኢሕአዴግ ጠቅላላ ጉባዔ አዳማ ከተማ ተስብስቦ ያፀደቃቸውን ዕቅዶች አፈጻጸም፣ በተለይ አዳማ ላይ ለተካሄደው ጉባዔ የቀረበው የሁለት ዓመት የፓርቲው ዕቅድ የአምስት ዓመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ መነሻ በመሆኑ በጥልቀት ይገመገማል ተብሏል፡፡  ከዚህ በተጨማሪ ነባር ታጋዮችን (አመራሮችን) በመተካካት መርሐ ግብሩ እየቀነሰ በወጣት ኃይል ለመተካት የተያዘውንም ዕቅድ ይገመገማል፡፡ የብአዴን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ አለምነህ መኮንን ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በብአዴን ደረጃ መተካካቱ በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ እየሄደ ነው፡፡ የተለወጠ ነገር የለም ሲሉ አስረድተዋል፡፡  በአሁኑ ወቅት የአራቱ ፓርቲዎች የበታች አመራሮች በስብሰባ ተጠምደዋል፡፡ ይህ የፓርቲዎቹ የታችኛው መዋቅር ስብሰባ የሚወክሉ የጠቅላላ ጉባዔ አባላትን መርጦ ይልካል፡፡ የተመረጡት የፓርቲዎቹ ጠቅላላ ጉባዔ አባላት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን ይመርጣሉ፡፡ ማዕከላዊ ኮሚቴዎቹ ናቸው ቀደም ሲል ዘጠኝ የኢሕአዴግ ሥራ አ