Posts

ኢህአዴግ ቀጣዩን ሊቀመንበር ሊመርጥ ነው

Image
የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ዘጠነኛ ድርጅታዊ ጉባዔውን ከወር በኋላ በባህርዳር ከተማ የሚያካሂድ ሲሆን በዚህ ጉባዔ ላይ የድርጅቱን ቀጣይ ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበሩን በመምረጥ ይፋ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የኢህአዴግ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን ከትናንት በስቲያ በጽ/ቤቱ ለጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፤ የግንባሩ ጉባዔ ዘንድሮ የሚካሄደው በሁለት ዓመት ተኩል ጊዜው ሲሆን ቀጣይ የኢህአዴግ ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበር በምክር ቤቱ ከተመረጡ በኋላ ይፋ ይደረጋል ብለዋል፡፡ “በመለስ አስተምህሮዎች ጠንካራ ድርጅትና የልማት ሃይሎች ንቅናቄ ለህዳሴያችን!” በሚል መሪ ቃል ይካሄዳል በተባለው ድርጅታዊ ጉባዔ፤ በኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚና በኢህአዴግ ምክር ቤት ውይይት ተደርጐበት የፀደቀው ረቂቅ ሪፖርት እንደሚፀድቅና አዲስ የቁጥጥር ኮሚሽን አባላትም እንደሚሰየሙ አቶ ሬድዋን ተናግረዋል፡፡ ጉባዔው የግንባሩ መሥራችና እስከህልፈተ ህይወታቸው ድረስ ድርጅቱን በሊቀመንበርነት ሲመሩ የነበሩት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሌሉበት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄድ መሆኑንም አቶ ሬድዋን ገልፀዋል፡፡ ግንባሩ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ህልፈት የተፈጠረውን የአመራር ክፍተት በተረጋጋ መንገድ መሙላቱን የጽ/ቤት ኃላፊው ጨምረው ገልፀዋል፡፡ በግንባሩ የጀመረው የአመራር መተካካት ሂደት በዘንድሮው ጉባዔ ትኩረት የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን የተናገሩት አቶ ሬድዋን፤ የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር ደረጃ በደረጃ የሚተካካበትና አዲሱ የአመራር ትውልድ ወደፊት የሚወጣበት እርምጃ እንደሚወሰድም ገልፀዋል፡፡ በጉባዔው ላይ ከአስራአምስት የውጭ አገራት የሚጋበዙ ፓርቲዎች እንደሚሳተፉበትና በአጠቃላይ ከ2500 በላይ ተሳታፊዎች ይገኙበታል

Speech Recognition System: Speaker Dependent Recognizer for Sidama Language

Speech recognition systems have been applicable in wide areas as various speech recognition methodologies, techniques and tools have been developed and implemented to generate a natural and intelligible speech. In this regard, this work attempts the possibility of developing a prototype speech recognition system for Sidama language using Hidden Marcov Model. The study has conducted extensive study on the language features, the components, speech recognition tools; the techniques used in speech recognition design, and identified those component that are dependent on the characteristics of language. Finally this work has showed a working prototype speech recognizer for the language, tested the performance of the system and compared its accuracy, and recommended measures for similar researches and projects. This work, therefore, will be useful to researchers, Speech application developers, Educators and other individuals or institutions working on similar projects. http://books.google.

The Sidama nation must Unanimously Reject the Sidama's '812' traitors and vehemently detest being called direction 'Debub'!!

February 22, 2013, Kukkissa, Sidama Reporter from Sidama Capital Hawassa, Misnomer Sidamo and Debub!! The Sidama didn't call itself Sidamo or Debub in its history!! Both were fabricated by the successive northern rulers, the muisnomer that lingers to this date. Under the current very regime, the regime that for the first time theoretically proclaimed rights of nations and nationalities to regional self determination and beyond up to independence; the Sidama nation merged into the pressure cooker known as Debub-the forced amalgamation the rulers have created to protect their politico-economic interests since their inception-nothing else!!! In the case of the Sidama nation in particular, the regime that is led by Sidama nation's fundamental enemies is implementing its policies through Sidama traitors cadres- all of whom trade by the Sidama nation's names!! At this very historical juncture, the Sidama nation needs to know who are friends and foes alike to be able to defend its

«የጊዳቦ መስኖ ግድብ ግንባታ በተያዘው ዓመት ይጠናቀቃል»-ኢንጂነር ብሥራት ደምሴ የጊዳቦ መስኖ ግድብ ሥራ ፕሮጀክት የሥራ ሂደት ባለቤት

Image
በአካባቢው እዚህም እዚያ ዛፎች ቁጥቋጦዎች በብዛት ይታያሉ። አልፎ አልፎ ከሚታዩ መለስተኛ ኮረብታዎች በስተቀር አካባቢው ሜዳማ ነው። በስፍራው ባሉት ሁለት መለስተኛ ኮረብታዎች መካከል የጊዳቦ ወንዝ ሰንጥቆ ያልፋል። በእዚህ ሥፍራ የጊዳቦ የመስኖ ግድብ ግንባታ እየተካሄደ ይገኛል። ትልልቅ ገልባጭ ተሽከርካሪዎች ያለፋታ አሸዋ ያራግፋሉ። አፈር ይጭናሉ፤ ጠጠር ይደፋሉ። ኤክስካቫተሮች፣ ሎደሮችና ሌሎች ማሽነሪዎች በየሥፍራው ይቆፍራሉ። ይጠርጋሉ። ያስተካክላሉ። ይደመድማሉ። ሠራተኞች በሥራ ተጠምደዋል። ከፊሎቹ አርማታ ይሞላሉ። የተወሰኑት ማሽነሪዎችን በማንቀሳቀስ ለሥራው የሚያስፈልጉ ግብአቶችን ያቀርባሉ። ሁሉም ሠራተኞች የአካባቢው ሙቀት ሳይበግራቸው ጥድፊያ ላይ ናቸው። በጊዳቦ የመስኖ ግድብ ግንባታ ለማፋጠን  24  ሰዓት ሥራው አይቋረጥም። በሌሊት በየሥፍራው ያሉት ትልልቅ ፓውዛዎች ጨለማውን ገፈው ብርሃን አላብሰው ታል። በሌሊቱ ግማሾቹ ሠራተኞች ሲያርፉ ቀሪዎቹ ሌሊቱን በሙሉ ሲሰሩ ያነጋሉ። የጊዳቦ የመስኖ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባለቤትነት በአማካሪው የውሃ ሥራዎች ዲዛይንና ቁጥጥር ድርጅት እና በውሃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ተቋራጭነት በኦሮሚያና በደቡብ አጐራባች ክልሎች ውስጥ ከ 13 ሺ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት የሚገነባ ፕሮጀክት ነው። ግድቡ የሚገነባው በጊዳቦ ወንዝ ላይ ነው። ፕሮጀክቱ መንግሥት በመደበው ከ 258  ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነባ ይገኛል። ይህ ፕሮጀክት ከተጀመረ ከሁለት ዓመት በላይ እንደሆነው የሚገልጹት በውሃ ሥራዎች ዲዛይንና ቁጥጥር ድርጅት የፕሮጀክቱ አማካሪ መሐንዲስ ኃላፊ ኢንጂነር ብርሃኑ ውቤ ናቸው። እሳቸው እንዳሉት በፕሮጀክት ግንባታው የግድብ፣ የትርፍ ውሃ ማስወገጃ የተያዘ ውሃ

ሲዳማ ኔት ኮሌጅ የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት ፌስቲቫል በመሳተፍ ላይ ነው

ለአራተኛ ጊዜ የሚካሄደው የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት ፌስቲቫል ቅዳሜ በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚጀመር አዘጋጁ አስታወቀ። የፌስቲቫሉ አዘጋጅ የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማኀበር ትናንት በሴንትራል ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቀው፤ አራተኛው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት ፌስቲቫል ቅዳሜ የካቲት  16  ቀን  2005 ዓ . ም በአዲስ አበባ ስታዲየም በድምቀት ይጀመራል። ይሄው መታሰቢያነቱ ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የተሰጠው የ 2005 ዓ . ም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ከደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች፣ ከኦሮሚያና ትግራይ ክልሎች አምስት እንዲሁም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተውጣጡ አሥራ አምስት በድምሩ ሃያ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተሳታፊ እንደሚሆኑ ማኀበሩ ገልጿል። በስፖርት ፈስቲቫሉ ማኀበሩ በዘጠኝ የስፖርት ዓይነቶች ውድድር እንዲደረግ ዝግጅት ቢያደርግም ተሳታፊ ተቋማቱ በስምንቱ ብቻ ለመሳተፍ በመመዝገባቸው በእነዚሁ ስፖርቶች ውድድሩ እንደሚካሄድ የማኀበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አብነት ግርማዬ አስታውቀዋል። ለአሥራ ሦስት ቀናት በሚቆየው በዚህ የስፖርት ፌስተቫል ለመሳተፍ ከክልሎች ለሚመጡ ስፖርተኞች በሴንትራል ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ሾላ ካምፓስ ማረፊያ መዘጋጀቱንም ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል። በስፖርት ፌስቲቫሉ ላይ ሃያዎቹን ተቋማት የወከሉ ሦስት ሺ የሚጠጉ ስፖርተኞች ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አቶ አብነት አስረድተዋል። ለፌስቲቫሉ ስኬት ፌዴራል ስፖርት ኮሚሽንና የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ከፍተኛ አስተዋጽዖ ማድረጋቸውን የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ ለዚህ ተግባራቸውም በኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህር