Posts

«የጊዳቦ መስኖ ግድብ ግንባታ በተያዘው ዓመት ይጠናቀቃል»-ኢንጂነር ብሥራት ደምሴ የጊዳቦ መስኖ ግድብ ሥራ ፕሮጀክት የሥራ ሂደት ባለቤት

Image
በአካባቢው እዚህም እዚያ ዛፎች ቁጥቋጦዎች በብዛት ይታያሉ። አልፎ አልፎ ከሚታዩ መለስተኛ ኮረብታዎች በስተቀር አካባቢው ሜዳማ ነው። በስፍራው ባሉት ሁለት መለስተኛ ኮረብታዎች መካከል የጊዳቦ ወንዝ ሰንጥቆ ያልፋል። በእዚህ ሥፍራ የጊዳቦ የመስኖ ግድብ ግንባታ እየተካሄደ ይገኛል። ትልልቅ ገልባጭ ተሽከርካሪዎች ያለፋታ አሸዋ ያራግፋሉ። አፈር ይጭናሉ፤ ጠጠር ይደፋሉ። ኤክስካቫተሮች፣ ሎደሮችና ሌሎች ማሽነሪዎች በየሥፍራው ይቆፍራሉ። ይጠርጋሉ። ያስተካክላሉ። ይደመድማሉ። ሠራተኞች በሥራ ተጠምደዋል። ከፊሎቹ አርማታ ይሞላሉ። የተወሰኑት ማሽነሪዎችን በማንቀሳቀስ ለሥራው የሚያስፈልጉ ግብአቶችን ያቀርባሉ። ሁሉም ሠራተኞች የአካባቢው ሙቀት ሳይበግራቸው ጥድፊያ ላይ ናቸው። በጊዳቦ የመስኖ ግድብ ግንባታ ለማፋጠን  24  ሰዓት ሥራው አይቋረጥም። በሌሊት በየሥፍራው ያሉት ትልልቅ ፓውዛዎች ጨለማውን ገፈው ብርሃን አላብሰው ታል። በሌሊቱ ግማሾቹ ሠራተኞች ሲያርፉ ቀሪዎቹ ሌሊቱን በሙሉ ሲሰሩ ያነጋሉ። የጊዳቦ የመስኖ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባለቤትነት በአማካሪው የውሃ ሥራዎች ዲዛይንና ቁጥጥር ድርጅት እና በውሃ ሥራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ተቋራጭነት በኦሮሚያና በደቡብ አጐራባች ክልሎች ውስጥ ከ 13 ሺ ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት የሚገነባ ፕሮጀክት ነው። ግድቡ የሚገነባው በጊዳቦ ወንዝ ላይ ነው። ፕሮጀክቱ መንግሥት በመደበው ከ 258  ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነባ ይገኛል። ይህ ፕሮጀክት ከተጀመረ ከሁለት ዓመት በላይ እንደሆነው የሚገልጹት በውሃ ሥራዎች ዲዛይንና ቁጥጥር ድርጅት የፕሮጀክቱ አማካሪ መሐንዲስ ኃላፊ ኢንጂነር ብርሃኑ ውቤ ናቸው። እሳቸው እንዳሉት በፕሮጀክት ግንባታው የግድብ፣ የትርፍ ውሃ ማስወገጃ የተያዘ ውሃ

ሲዳማ ኔት ኮሌጅ የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት ፌስቲቫል በመሳተፍ ላይ ነው

ለአራተኛ ጊዜ የሚካሄደው የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት ፌስቲቫል ቅዳሜ በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚጀመር አዘጋጁ አስታወቀ። የፌስቲቫሉ አዘጋጅ የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማኀበር ትናንት በሴንትራል ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቀው፤ አራተኛው የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት ፌስቲቫል ቅዳሜ የካቲት  16  ቀን  2005 ዓ . ም በአዲስ አበባ ስታዲየም በድምቀት ይጀመራል። ይሄው መታሰቢያነቱ ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የተሰጠው የ 2005 ዓ . ም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ከደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች፣ ከኦሮሚያና ትግራይ ክልሎች አምስት እንዲሁም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተውጣጡ አሥራ አምስት በድምሩ ሃያ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተሳታፊ እንደሚሆኑ ማኀበሩ ገልጿል። በስፖርት ፈስቲቫሉ ማኀበሩ በዘጠኝ የስፖርት ዓይነቶች ውድድር እንዲደረግ ዝግጅት ቢያደርግም ተሳታፊ ተቋማቱ በስምንቱ ብቻ ለመሳተፍ በመመዝገባቸው በእነዚሁ ስፖርቶች ውድድሩ እንደሚካሄድ የማኀበሩ ፕሬዚዳንት አቶ አብነት ግርማዬ አስታውቀዋል። ለአሥራ ሦስት ቀናት በሚቆየው በዚህ የስፖርት ፌስተቫል ለመሳተፍ ከክልሎች ለሚመጡ ስፖርተኞች በሴንትራል ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ሾላ ካምፓስ ማረፊያ መዘጋጀቱንም ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል። በስፖርት ፌስቲቫሉ ላይ ሃያዎቹን ተቋማት የወከሉ ሦስት ሺ የሚጠጉ ስፖርተኞች ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አቶ አብነት አስረድተዋል። ለፌስቲቫሉ ስኬት ፌዴራል ስፖርት ኮሚሽንና የአዲስ አበባ ስፖርት ኮሚሽን ከፍተኛ አስተዋጽዖ ማድረጋቸውን የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ ለዚህ ተግባራቸውም በኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህር

በመካከለኛው የኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ አካባቢ የነዳጅ ልማትና ፍለጋ ሊካሂድ ነው

Image
አዲስ አበባ ፣ የካቲት 14፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) አፍሪካ ኦይል ኮርፖሬሽን በመካከለኛው የኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ አካባቢ የነዳጅ ልማትና ፍለጋ ሊያካሂድ ነው። የማዕድን ሚኒስቴርና ኩባንያው በፍለጋው ላይ ዛሬ የስምምነት ሰነድ ተመፈራርመዋል። በፊርማው ወቅትም የማዕድን ሚኒስትሯ ወይዘሮ ስንቅነሽ እጅጉ ነዳጅ ፈላጊ ኩባንያው በሃገሪቱ ጥናቶችን ሲያደርግ እንደመቆየቱና በሌሎች ሃገራትም ስኬታማ ስራዎችን እንደመስራቱ ፥  ፍለጋው ውጤታማ ይሆናል ብለን እናምናለን ብለዋል። የኩባንያው ዋና ስራ አስፈጻሚ ጀምስ ፍሊፕስ ደግሞ በኢትዮዽያም ተስፋ ሰጪ ጥናቶችን አካሂደናል ወጤታማ እንደምንሆነም እምነታችን ነው ብለዋል ። ከቱሎው ኦይል ጋር በጋራ እያካሄድን ያለው ቁፋሮም በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ በመሆኑ በአጭር ጊዜ ውጤቱን እናሳውቃለን ብለዋል ። በእመርታ አስፋው

አሮሬሳ ወረዳ የ119 ሺህ 874 ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ከጃፓን መንግሥት ኣገኘ

Image
አዲስ አበባ የካቲት 13/2005 ጃፓን በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚካሄዱ የማኅበረሰብ ልማት ሥራዎች የሚውል ከ581 ሺህ ዶላር በላይ ለአራት መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ለሲዳማ ዞን አስተዳደር ዛሬ ድጋፍ አደረገች። የልማት ሥራዎችን ለማከናወን ከጃፓን መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ የተደረገላቸው በትግራይ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በሐረር ክልል ለሚገኙ የልማት ማኀበራትና ድርጅቶች እንዲሁም ለሲዳማ ዞን አስተዳዳር ነው። በድጋፍ የተገኘው ገንዘብ በአራቱ ክልሎች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ማኅበረሰቦች የትምህርት ቤቶች ማስፋፋያ፣ ንጹህ የመጠጥ ውኃ ግንባታና ለጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማት ግንባታ የሚውል ነው። የጃፓን መንግሥት በድጋፍ ከሰጠው ገንዘብ ውስጥ 122 ሺህ 229 ዶላር በከንባታ ጠንባሮ ዞን ውስጥ ለሙዱላ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ሲውል 119 ሺህ 874 ዶላር ደግሞ በሲዲማ ዞን አሮሬሳ ወረዳ ለሚገኝ ትምህርት ቤት ግንባታና ቁሳቁስ ማሟያ እንደሚውል ተገልጿል። እንዲሁም 118 ሺህ 575 ዶላር በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ለማንዱራ ወረዳ ለትምህርት ቤትና የአስተዳደር ቢሮ ግንባታ የሚውል ሲሆን 116 ሺህ 208 ዶላር ደግሞ በሐሪር ክልል ለድሬ ጢያራና ለሶፊ ወረዳ ለንጹህ የመጠጥ ውኃ ግንባታ ይውላል።  ቀሪው 104 ሺህ 689 ዶላር ደግሞ በትግራይ ክልል ለእንደርታና ለክልት አውላዕሎ ወረዳ ንጹህ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች ማከናወኛ የሚውል ሲሆን ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ ከ5 ሺህ በላይ አባወራዎችን ተጠቃሚ ያደርጋሉ። በኢትዮጵያ የጃፓን ኤምባሲ ጉዳይ አስፈፃሚ ሚስተር ሃጂሜ ኪታኦካ በኤምባሲው በተካሄደው የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደገለጹት የትምህርት ተቋማቱና የንጹህ የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች ግንባታ ሲጠናቀቅ በአጠቃላይ ከ15 ሺህ በላይ የአካ

የክልሉ ምክር ቤት ሶስተኛ ዓመት አራተኛ ዙር ስድስተኛ መደበኛ ጉባኤ በሃዋሳ ከተማ እንደቀጠለ ነው

Image
በደቡብ   ብሄር   ብሄረሰቦችና   ህዝቦች   ክልል   በበጀት አመቱ   አጋማሽ   በየዘርፉ የተከናወኑ   ተግባራት   አበረታች   ውጤት   የተመዘገበባቸው   መሆኑን   የክልሉ   ርዕሰ መስተዳድር   አስታወቁ   ። የክልሉ   ምክር   ቤት   ሶስተኛ   ዓመት   አራተኛ   ዙር   ስድስተኛ   መደበኛ   ጉባኤ   በሃዋሳ ከተማ   እየተካሄደ   ነዉ   ።ርዕሰ   መስተዳድሩ   አቶ   ሽፈራው   ሽጉጤ   የክልሉን   የግማሽ በጀት   ዓመት   የዕቅድ   አፈጻጸም   ሪፖርት   ለምክር   ቤቱ   ባቀረቡበት   ወቅት   እንዳሉት  በየስራ   ዘርፉ   ካለፈዉ   ዓመት   ክንውን   ምርጥ   ተሞክሮዎችን በመውሰድና   በማስፋት   ስትራተጂ   በመጠቀም   ውጤታማ   ተግባራት   ተከናውነዋል   ። በመንግስትና   በህብረተሰቡ   የተሟላ   ተሳትፎ   የኪራይ   ሰብሳቢነትን   ችግሮችን   ለመቅረፍ   በሚያሰችል   መልኩ   በገጠርና   በከተማ   የተለያዩ   ተግባራትን በማከናወን   ለውጥ   ማምጣት   የተቻለ   መሆኑን   አስታዉቀዋል   ። ባለፉት   ስድስት   ወራት   በግብርና   ልማት፣   በመንገድ   ግንባታና   በቀበሌ   ተደራሽ   መንገድ   ስራዎች   የገጠር   ቀበሌዎችን   ዕርስ   በዕርስና   ከዋና   መንገድ ጋር   በማገናኘት  705  ኪሎ   ሜትር   መንገድ   ተገንብቶ   መጠናቀቁን የገለፁት አቶ ሽፈራው በዚህም   አርሶና   አርብቶ   አደሩ   ምርቱን   ለገበያ   በማቅረብ ተጠቃሚ   መሆኑን   አመልክተዋል   ። መንገዶቹ   በሚገነቡባቸው   አካባቢዎችም   በማህበር   ለተደራጁና   በጉልበት   ሰራ   ለተሰማሩ   ከ 106  ሺህ   በላይ   ሰዎች   የስራ   ዕድል   መፈጠሩን