Posts

የ2005 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮና የካቲት 17 ይጀመራል ፤የያዝነውን አመት ፕሪሚየር ሊግ ሀዋሳ ከነማ በ19 ነጥብ ይመራል

በአፍሪካ ዋንጫ ምክንያት ለሳምንታት ተቋርጦ የቆየው የ2005 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በመጪው የካቲት 17 እንደሚጀመር ፌዴሬሽኑ አስታወቀ፡፡ በእለቱ ከሚከናወኑት የ10ኛ ሳምንት ግጥሚያዎች መካከል ኢትዮጵያ ቡና ከደደቢት፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከመከላከያ የሚያካሂዷቸው ጨዋታዎች ከፍተኛ ግምት ተሰጥቷቸዋል፡፡ የያዝነውን አመት ፕሪሚየር ሊግ ሀዋሳ ከነማ በ19 ነጥብ ይመራል፡፡ ደደቢት በ18 ነጥብና በ9 ተጨማሪ ግብ ሁለተኛ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ በተመሳሳይ ነጥብና በ6 ግብ ክፍያ ሶስተኛ፣ ኢትዮጵያ ቡና በ16 ነጥብ 4ኛ ሆነው ይከተላሉ፡፡ በዘንድሮዉ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ለፍጻሜ ግማሽ የደረሱት ቡድኖች በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮናና ኮንፌዴሬሽን ካፕ የሚሳተፉት ቅዱስ ጊዮርጊስና ደደቢት የመልስ ጨዋታቸውን የካቲት 23 እና 24 አዲስ አበባ ስታዲየም ካከናወኑ በኋላ ለማካሄድ መታቀዱንም ፌዴሬሽኑ አስታውቋል፡፡ በተመሳሳይ የሴቶች ምድብ ጥሎ ማለፍ በመጪው የካቲት 10/2005 ይካሄዳል፡፡ ኢትዮጵያ ቡና ከአርባምንጭ ፣ ደደቢት ከቅዱስ ጊዮርጊስ አዲስ አበባ ላይ ይጫወታሉ፡፡ ሙገር ከአዳማ ፣ ሐረር ቢራ ከመብራት ሃይል ፣ ሐዋሳ ከነማ ከመከላከያ በዕለቱ የሚከናወኑ ግጥሚያዎች ናቸው ፡፡ የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መለስ ዋንጫ በምድብ አንድ ደደቢት በ18 ነጥብ ፣ኢትዮጵያ መድህን 12 ነጥብ፣ በምድብ ሁለት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ16፣ መከላከያ በ11፣ በምስራቅ ምድብ አዳማ ከነማ በ15፣ ድሬደዋ ከነማ በ12፣ በደቡብ ምድብ ሀዋሳ ከነማ በ9 ነጥብና በ6 ተጨማሪ ግብ ሲዳማ ቡና ፣ አንደኛና ሁለተኛ በመሆን ምድቡን በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡

በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የቡና ግብይት ጥያቄ አስነስቷል

በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የቡና ግብይት ጥያቄ አስነስቷል Форум вебмастеров •    ኤክስፖርተሮች የገዙትን ቡና በጥራት ደረጃው ማግኘት አልቻሉም •    ንግድ ሚኒስቴር ችግሩን ደርሼበታለሁ ብሏል  የአገሪቱን የግብይት ሥርዓት ዘመናዊ ለማድረግ ከአምስት ዓመት በፊት ሥራ የጀመረውና ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ዝናን ያተረፈው የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ድርጅት (ኢሲኤክስ) የተዝረከረከና ሕገወጥ አሠራር እየተንሰራፋበት መሆኑን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡ መንግሥት በገበያ ማዕከሉ የሚስተዋለውን አሳሳቢ ችግር ደርሼበታለሁ፤ በሕገወጥ ሥራ ተሰማርተው በተገኙ ሠራተኞች ላይም ዕርምጃ እየወሰድኩ ነው ይላል፡፡ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ በቡና ኤክስፖርት ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የገበያ ማዕከሉ በሚያስተዳድራቸው የቡና መጋዘኖች ውስጥ የቡና ቅሸባ ተንሰራፍቷል፡፡ ይህም ከውጭ አገር ደንበኞች ጋር እያጋጫቸው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የገበያ ማዕከሉ ከአገር ወስጥ አቅራቢዎች ቡናን በመረከብ የቡናውን ናሙና በመውሰድ የቀረበው ምርት የኤክስፖርት ደረጃን ማሟላት አለማሟሟላቱን ካረጋገጠ በኋላ፣ ላኪዎች እንዲጫረቱበት ያደርጋል በማለት የግብይት ሥርዓቱን የሚናገሩት እነዚሁ ቅሬታ አቅራቢዎች፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በዚህ የግብይት ሥርዓት ውስጥ አሳሳቢ ችግሮች እየተስተዋሉ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ በግብይት ሥርዓቱ መሠረት የኤክስፖርት ደረጃን አሟልቷል የተባለ ቡና ጨረታን ካሸነፉ በኋላ ምርቱን ወደ ውጭ ለመላክ ያሸነፉበትንና የከፈሉበትን ማስረጃ በመያዝ ወደ ገበያ ማዕከሉ መጋዘኖች በሚሄዱበት ወቅት፣ የቡና ምርቱን በደረጃው እንደማያገኙ ከዚህ በተጨማሪም የከፈሉበት የቡና ምርት ከመጠኑ አንሶ እንደሚያገኙት ተናግረዋል፡፡ ይህም ከውጭ ገዥዎች ጋር እያጋ

ዘመቻ መለስ በሲዳማ

Image
የዘመቻውን መጀመር በተመለከተ የደቡብ ቲቪ የተዘጋጀ ፕሮግራም

Hawassa - City of 'Amour'

Image
"Amour" is a French word, which means love in English. Many people call French a language of romance that is apt enough to express love and passion. That is why the writer of this piece preferred the French word "Amour" to the English world "love" to vent the strong emotion of love the city of Hawassa is associated with. The writer of this article had recently been to the city of Hawassa, one of the most glamorous cities in Ethiopia, which exhibits rich cultural diversity and heritage, well preserved scenery, flavorful city delicacies and magnificent people from different ethnic communities of the country. Hawassa is a city located on the shores of Lake Hawassa in the Great Rift Valley. It is situated some 270_km south of Addis Ababa via Bishoftu in the Sidama Zone, Southern Nations, Nationalities and Peoples' State. It is 130_km east of Sodo, 75_km north of Dilla and 1,125_km north of Nairobi. The city lies on the Trans-African Highway 4 Cairo

የወንዶገነት ደንና አሳሳቢ የሥነ ምህዳር ቀውሶች

Image
ከአዲስ አበባ 250 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ወደምትገኘው ሻሸመኔ ከተማ ሲደርሱ ቀኙን ትተው ወደ ግራ ሲታጠፉ አንድ አረንጓዲያማ አካባቢ የሚያደርሰውን አስፋልት  ያገኛሉ፡፡ ከዚያም 11 ኪ.ሜ እንደተጓዙ በአገራችን የመጀመሪያው በደን የተሸፈነ ስፍራና በአገሪቱ ብቸኛው  የደንና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ይደርሳሉ፡፡ ቀጥሎም በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች መዳረሻ ወደሆነው ዋቢሸበሌ መዝናኛ ሆቴል ከሦስት ኪ.ሜ ጉዞ በኋላ ያገኛሉ፡፡ በአሳብ ይዤአችሁ  የምወስዳችሁ ሥፍራ ወንዶ ገነት ይባላል፡፡ እነዚህን ከላይ የዘረዘርኳቸው ስፍራዎች ከ30 ዓመታት በፊት በነበሩበት ማራኪ የተፈጥሮ ውበታቸው ጋር ማየት በእርግጥ የማይቻል በመሆኑ የሰነድና የስው አስረጅ ካላገኙ የቀድሞውን ታሪክ ማወቅ አስቸጋሪ ይሆንቦታል፡፡ በአገሪቱ በደን ሽፋንና በተፈጥሮ መስህብ የማንንም ቀልብ የመግዛት አቅም የነበረው ስፍራ ዛሬ ትዝታ የመሆኑ ምስጢርና ተያያዥ የሥነ ምህዳር ችግሮች ሰለባ ሆኗል፡፡ ወንዶገነትና የአረንጓዴው ዘመቻ በ1970ዎቹ መጀመሪያ በደርግ የሥልጣን ዘመን የአረንጓዴው ዘመቻ ደን ሠርቶ ማሳያ ማዕከል የነበረው ወንዶገነት ከተፈጥሮ ጫካ በተጨማሪ የባሕር ዛፍና ጥድ እንዲሁም ሌሎች ዛፎች የተሸፈነ እጅግ ማራኪ ስፍራ ነበረ፡፡ በወቅቱ  በስዊድናውያን ዕርዳታ የተቋቋመው የደን ኮሌጅ ዓላማም ከአካባቢው ባለፈ በአገሪቱ የደን ሀብትን ማስፋፋት ስለነበረ የወረዳው ዙርያ በዛፎች እንዲሸፈን ተደርጓል፡፡ ከነዚህም አካባቢዎች ዛሬ የጫት ማሳ ሆነው የቀሩትንና የቀድሞውን መላጌ ወንዶ ሥጋ ፋብሪካ (አሁኑ ኤልፎራ) የሚገኝባቸው ቀበሌዎችን ያካትታል፡፡ የደን ኮሌጅ ከሚገኝበት ሆሻ ከተማ ዙሪያውን ስድስት ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘውን ሌላ ትንሽ ከተማ ኬላና በ