Posts

በሲዳማ ዞን ቦርቻ ወረዳ የኣፈር መልሶ የማልማት ስራ የተመለከተ የቲቪ ፕሮግራም

Image
TV Programe - Sidama Zone Borricha Woreda Soil Rehabilitation Activities.

Delightful Public Lecture by the Indonesian Ambassador to Ethiopia.

Image
Indonesian ambassador to Ethiopia, H.E. Ambassador Ramli Saud gave a public lecture to community of Hawassa University (HwU) on January 31, 2013. On the occasion, Dr. Yosef Mamo, President of HwU following his brief about his University under scored the importance of making collaboration with Asian counties like Indonesia which are leading the world economy and known for making their partnership on the basis of mutual benefit. In his lecture, the ambassador highlighted the historical back ground of the two countries relation. Of the significant progress made in their relation, according to the ambassador’s lecture, the trade relation is worth mentioned, i.e. the total trade relation which was US $ 40.7 mil in 2004 grew up surprisingly to $303.9 in 2012. The ambassador also witnessed that Ethiopia has shown a magnificent progress in many aspects and believes that it is the most secured country in Africa.  The Ambassador also told that academic institutions of his country offer

የእለቱ የሲዳማ ዞን ዜና በደቡብ ቲቪ 2/6/2013

Image
http://www.youtube.com/watch?v=NfHARRtr_k4

በሲዳማ ዞን የማጅራት ገትር ወረርሽን ተከስቷል

Image
አዲሰ አበባ ፣ ጥር 29 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ላይ የተከሰተውን የማጅራት ገትር በሽታ በቁጥጥር ስር ለማዋል የተጠናከረ ጥረት እየተደረገ ነው ። በአስር አመት አንድ ጊዜ የሚከሰተው የማጅራት ገትር (ማኔንጃይትስ) ወረርሽኝ ፥ ሰሞኑን በደቡብ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ላይ ተከስቶ እንደነበር ነው መረጃዎች የሚያሳዩት። ከእነዚህም ውስጥ በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ፣ በጋሞ ጎፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማና አላባ አካባቢ ፥ ከ100 በላይ ምልክቶቹ የታየባቸው ሰዎች በላቦራቶሪ ምርመራ በበሽታው መያዛቸውን ማረጋገጥ ተችሏል ነው ያለው የክልሉ ጤና ቢሮ። በሽታው ከመከሰቱ በፊት ህብረተሰቡ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ፥ የተለያዩ መንገዶችን በመጠቀም የማስተማር ስራ መሰራቱን በጤና ቢሮው የህዝብ ግንኙነትና የጤና ኮሚዩኒኬሽን የስራ ሂደት ባለቤት አቶ ቀድርላ አህመድ ተናግረዋል። በሽታው ተከስቶባቸዋል ተብሎ የተረጋገጡ ቦታዎች ላይ አስፈላጊው የመከላከል ስራ እየተሰራ እንደሆነ ጠቅሰው ፥ በሽታውን ለመቆጣጠር ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ ነው ብለዋል። ወረርሽኙ ወደ ሌሎች የክልሉ አካባቢዎች እንዳይዛመት  የበሽታው መመርመሪያ ማሽን በክልሉ በስፋት ተሰራጭቶ ስራዎች እየተሰሩ ነው ያሉት። በሽታው በተከሰተባቸው አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች በስጋት ያልተጣራ መድሃኒት እየወሰዱ በመሆናቸው ፥ በዚህ ዙሪያም አስፈላጊ ጥንቃቄ ህብረተሰቡ እንዲያደርግ ነው የጠየቁት። ማህበረሰቡ ወደ ሌሎች አካባቢዎችም ይዛመታል ከሚል ከስጋት ነጻ ይሆን ዘንድም በሽታውን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያግዙ መድሃኒቶች በስፋት እየተሰራጩ እንደሆነም ይናገራሉ። ከቅድመ መከላከል ባለፈም በአርባምንጭ ከተማ ብቻ

አርቲስቲክ ማተሚያ ድርጅት አዳዲስ አገልግሎቶችን እየሠጠ ነው

አርቲስቲክ ማተሚያ ድርጅት የምስጢራዊ ህትመት፣ የማማከር፣ ጥገና፣ የግራፊክ ዲዛይንና ፕሌት ቀረፃ እንዲሁም የህትመት ቴክኖሎጂ ሥልጠና አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። ድርጅቱ የተመሰረተበትን  82 ኛ ዓመቱንና የሐዋሳ ቅርንጫፍ የተቋቋመበትን ስድስተኛ ዓመት ምስረታ በዓልን እንዲሁም የደንበኞች ቀንን በሐዋሳ ከተማ አክብሯል ። በከተማዋ ሌዊ ሆቴል ከደንበኞች ጋር የፓናል ውይይት ባካሄደበት ወቅት የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተካ አባዲ እንደተናገሩት፤ ድርጅቱ በኢትዮጵያ ብቸኛው የህትመት ቴክኖሎጂ ሥልጠና በመስጠት ላይ የሚገኝ ተቋም ነው ። ድርጅቱ በእስካሁኑ ሂደት ወደ  500  ያህል ሠልጣኞችን ያስመረቀ ሲሆን፤ ሁሉም ምሩቃን ወደ ሥራው ዓለም ተቀላቅለዋል። በጥቃቅንና አነስተኛ ለተደራጁ ምሩቃን ድርጅቱ የማሽንና የሌሎች መሳሪያዎች ድጋፍ ያደርጋል። እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ ድርጅቱ ከአዳዲስ አገልግሎቶች መካከል የምስጢራዊ ህትመት አገልግሎትን ጀምሯል። በእስካሁንም ሂደት ከሠራቸው ምስጢራዊ ህትመቶች መካከል የደቡብና የሐረሪ ክልልን እንዲሁም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች ፈተናን ለአብነት ጠቅሰዋል። ይህንንና ሌሎችንም ምስጢራዊ ህትመቶችን በቀጣይ አጠናክሮ እንደሚቀጥልበት አመልክተዋል። ድርጅቱ የግራፊክ፣ የዲዛይንና የፕሌት ቀረፃ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በተለይም በሰዓት እስከ አንድ ሺ ድረስ ፕሌት ማውጣት የሚችል ማሽን መግዛቱን ተናግረዋል። ማተሚያ ድርጅቱ ለተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የማማከርና የጥገና አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የበርካታ ዩኒቨርሲቲዎችን ማተሚያ ማሽኖች ለመጠገን የሚያስችሉ የጥገና ስምምነት መፈራረሙን ገልጸዋል። በቅርቡም የጥገና ሥራው እንደሚጀመርም ነው