Posts

አርቲስቲክ ማተሚያ ድርጅት አዳዲስ አገልግሎቶችን እየሠጠ ነው

አርቲስቲክ ማተሚያ ድርጅት የምስጢራዊ ህትመት፣ የማማከር፣ ጥገና፣ የግራፊክ ዲዛይንና ፕሌት ቀረፃ እንዲሁም የህትመት ቴክኖሎጂ ሥልጠና አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። ድርጅቱ የተመሰረተበትን  82 ኛ ዓመቱንና የሐዋሳ ቅርንጫፍ የተቋቋመበትን ስድስተኛ ዓመት ምስረታ በዓልን እንዲሁም የደንበኞች ቀንን በሐዋሳ ከተማ አክብሯል ። በከተማዋ ሌዊ ሆቴል ከደንበኞች ጋር የፓናል ውይይት ባካሄደበት ወቅት የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ተካ አባዲ እንደተናገሩት፤ ድርጅቱ በኢትዮጵያ ብቸኛው የህትመት ቴክኖሎጂ ሥልጠና በመስጠት ላይ የሚገኝ ተቋም ነው ። ድርጅቱ በእስካሁኑ ሂደት ወደ  500  ያህል ሠልጣኞችን ያስመረቀ ሲሆን፤ ሁሉም ምሩቃን ወደ ሥራው ዓለም ተቀላቅለዋል። በጥቃቅንና አነስተኛ ለተደራጁ ምሩቃን ድርጅቱ የማሽንና የሌሎች መሳሪያዎች ድጋፍ ያደርጋል። እንደ ዋና ዳይሬክተሩ ገለፃ ድርጅቱ ከአዳዲስ አገልግሎቶች መካከል የምስጢራዊ ህትመት አገልግሎትን ጀምሯል። በእስካሁንም ሂደት ከሠራቸው ምስጢራዊ ህትመቶች መካከል የደቡብና የሐረሪ ክልልን እንዲሁም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች ፈተናን ለአብነት ጠቅሰዋል። ይህንንና ሌሎችንም ምስጢራዊ ህትመቶችን በቀጣይ አጠናክሮ እንደሚቀጥልበት አመልክተዋል። ድርጅቱ የግራፊክ፣ የዲዛይንና የፕሌት ቀረፃ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በተለይም በሰዓት እስከ አንድ ሺ ድረስ ፕሌት ማውጣት የሚችል ማሽን መግዛቱን ተናግረዋል። ማተሚያ ድርጅቱ ለተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የማማከርና የጥገና አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቁመው፤ የበርካታ ዩኒቨርሲቲዎችን ማተሚያ ማሽኖች ለመጠገን የሚያስችሉ የጥገና ስምምነት መፈራረሙን ገልጸዋል። በቅርቡም የጥገና ሥራው እንደሚጀመርም ነው

በቅርቡ ሲዳማ ውስጥ የምካሄደውን የኣካባቢ ምርጫ ለማሸነፍ ብቸኛው ኣማራጭ የህዝቡን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎችን መመለስ ብቻ ነው

ከሁለት ወራት በኃላ በኢትዮጵያ ብሎም በሲዳማ የምከሄደው የኣከባቢ ምርጫ ላይ ለመሳተፊ ሃዋሳን ጨምሮ በሲዳማ ዞን ውስጥ ኣራት የምሆኑ የፖለቲካ ድርጅቶች ተመዝግበው የምርጫ ምልክት መውሰዳቸውን ከኣገሪቱ ምርጫ ቦርድ ሰምተናል። እነዚህ በሲዳማ እንወዳደራለን ብለው የምርጫ ምልክት የወሰዱት የፖለቲካ ፓርቲዎች የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ( ሲኣን ) ፤ ደኢህዴን _ ኢህኣዴግ፤ኢዴፓ እና ኢህኣፓ ናቸው። በነገራችን ላይ በምርጫ ቦርድ ኣደራጃጀት ሃዋሳ እና ሲዳማ የምል ክፍፍል የለም። በኣሁኑ ጊዜ ሃዋሳ እና ሲዳማ ተብለው የተከፋፈሉ ኣከባቢዎችን የምወክሉ ሰዎች በማንኛውም መንገድ የሲዳማ ተወላጆች መሆን ኣለባቸው። ምክንያቱ በዚህ ምርጫ ላይ ብቻ ሳይሆን በተለይ ከሶስት ኣመት በኃላ በምካሄደው ብሄራዊ ምርጫ በተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ የሲዳማን ብሄር የምወክሉ ግለሰቦች ከሁሉም የሲዳማ ኣካባቢዎች መምጣት ስላለባቸው ነው። ለምሳሌ ያህል ከሃዋሳ የምወከሉት ግለሰብ የሲዳማ ተወላጅ ካልሆኑ የሲዳማን ህዝብ በተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ የምወክሉት ተወካዮች ቁጥር ያሳንሳል በተጎዳኝ በሃዋሳ የምያሸንፈው የሌላ ብሄርሰብ ተወላጅ ለብሄረሰቡ ተጨማር የተወካይ ቁጥር ይጨምርለታል ማለት ነው። ይህ ማለት ቀድሞም ብሆን የሲዳማ ህዝብ ብዛት እና በተወካዮች ምክር ቤት ያለው ውክልና ተመጣጣኝ ኣይደለም የምል ኣመለካከት ያጠናክራል። ወደ ጉዳያችን ስንመለስ፤ በዚህ ጽሁፍ በኣራቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ ትኩረት ከመሰጠት ይልቅ በሁለቱ ላይ ማለትም በሲኣን እና በደኢህዴን ላይ ትኩረት ለመሰጠት ፈልጋለሁ። እስቲ እነዚህ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይዘው ነው የቀረቡ ? ለሲዳማ ህዝብ የምጠቅም ምን ይዘዋል ? በምሉት እና በሌሎች ጉዳዮች ላይ እንጫዎት። በኣጠቃላይ በኣገሪቱ ደረጃ ሲታይ ‹‹በግንባ

ያልተመለሱ አንገብጋቢ የምርጫ ጥያቄዎች

Image
ምርጫ መጥቶ በሄደ ቁጥር ላለፉት 22 ዓመታት በተደጋጋሚ የሚነሱ ጥያቄዎች አሉ፡፡ ‹‹በግንባታ ሒደት ላይ ነው›› የሚባለው የኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ከዜጎቹ፣ ከምሁራን፣ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ፍላጎት ካላቸው ሦስተኛ ወገን የውጭ አገር ተቋማትና አገሮች እንዲሁም ዜጎች፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎችና ከሌሎች አካላትና ግለሰቦች የሚነሱትን ጥያቄዎች በሒደት የመመለስ ፍላጎት ያለው አይመስልም፡፡ ለማቀራረብ እንኳን የሚከብደው ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ኢሕአዴግ የሚከተሉት ርዕዮተ ዓለም ላይ የሚቀርበው ጥያቄና የሚሰጠው ምላሽ አንዱ አንገብጋቢ ጉዳይ ነው፡፡ ይህ ርዕሰ ጉዳይ ኢሕአዴግና ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተቀራርበው ለመሥራት እንዳይችሉ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ሌላኛው ጥያቄ በኢሕአዴግና በመንግሥት መካከል ያለውን ግልጽ ያልሆነ ግንኙነት ወይም መቀላቀል ይመለከታል፡፡ ኢሕአዴግ የፓርቲውንና የመንግሥትን ሚና በመቀላቀልና ፓርቲው ያለአግባብ የመንግሥትን ሀብት እንዲጠቀም እንዳደረገው በተደጋጋሚ ቅሬታ እንዲቀርብበት በር ከፍቷል፡፡ የምርጫ ጉዳይ አስተዳዳሪ ተቋማትና በዲሞክራሲ ግንባታ ሒደቱ ላይ ከፍተኛ ሚና የሚጫወቱ ተቋማት ላይ የሚነሳው የነፃነትና የገለልተኝነት ጥያቄ ሌላው ጉዳይ ነው፡፡ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድና የመንግሥት የሚድያ ተቋማት አሁንም የዛሬ 18 ዓመት ይባሉ እንደነበረው ኢሕአዴግን ብቻ በማገልገል፣ በሕግ ሁሉንም ተወዳዳሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች በእኩልነት እንዲያገለግሉ የተጣለባቸውን ኃላፊነት እየተወጡ አይደለም ተብለው ይተቻሉ፡፡ ኢሕአዴግ በየትኛውም መስፈርት ጠንካራ ፓርቲ ነኝ ይላል፡፡ በአንፃሩ ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተጠናክረው በመተባበር በመሥራት ለኢሕአዴግ ፖሊሲዎች አማራጮች ከማቅረብና ደጋፊና የድጋፍ መሠረታቸውን ከማደላደል ይልቅ፣ እ

በሃዋሳ ከተማ በመገንባት ላይ ያለው የህጻናትና የአረጋዊያን ማዕከል ግንባታ ከ70 በመቶ በላይ ተጠናቀቀ

Image
ሃዋሳ ጥር 24/2005 በሃዋሳ ከተማ ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በመንግስትና በህብረተሰብ ተሳትፎ እየተሰራ ያለው የህጻናትና የአረጋዊያን ማዕከል ግንባታ ከ70 በመቶ በላይ መጠናቀቁ ተገለጠ ። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከሜሪ ጆይ ልማት ማህበር ጋር በመሆን በተለያዩ ማህበረሰብ አቀፍ ጉዳዮች ዙሪያ ተባብረው ለማስራት የሚያስችል የጋራ መግባቢያ ሰነድም መፈራረማቸው ተገልፀዋል፡፡፡፡ በክልሉ መንግስት፣ በህብረተሰብ ተሳትፎና በሌሎች የልማት አጋሮች ድጋፍ ከሁለት ዓመት በፊት የተጀመረው የህጻናትና የአረጋዉያን ማእከል ግንባታ ዉስጥ እስካሁን ከሰባ በመቶ በላይ ተጠናቋል ። የሃዋሳ ከተማ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያና የበጎ ፈቃደኞች ማህበር ሰብሳቢ አቶ ዘለቀ ከበደ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ከሃዋሳ ከተማ አስተዳደር በነፃ በተሰጠው ከ6ሺህ 400 ካሬ ሜትር በላይ ያለዉ ማእከል 22 የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ክፍሎች አሉት ። ማዕከሉ በዋናነት ቤተ መፃህፍት፣ የምክር አገልግሎት መስጫ /ካውንስልንግ/ የህክምና ክፍል፣ የመዝናኛ ፣ ዎርክሾፕና ሴራጅም እንዲሁም ሌሎች አገልግሎት መስጫዎች አካቶ የያዘ መሆኑን አስረድተዋል ማእከሉ ባለፉት ስድስት ዓመታት ከሜሪ ጆይ የልማት ማህበር ጋር በመተባበር በተለይም ሴት አረጋዊያንን በተለያዩ የገቢ ማስገኛ ስራዎች በማሳተፍ ከኢኮኖሚ ጥገኝነት እንዲላቀቁ ባከናወናቸዉ ስራዎች አበረታች ውጤት መመዝገቡ ተገልጧል ። የሜሪ ጆይ ልማት ማህበር መስራችና ስራ አስኪያጅ ሲስተር ዘብይደር ዘውዴ በበኩላቸው ማህበሩ በአዲስ አበባ እና በደቡብ ክልል 12 ከተሞች ለችግር የተጋለጡ ከ42ሺህ በላይ ህፃናትና 800 አረጋዉያን በቋሚነት የአልባሳት፣ የጤና፣የትምህርት፣የስነልቦና፣ የመጠለያ፣ የምግብና ሌሎች ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛ

በደቡብ ክልል ከአምስት ሚሊዮን የሚበልጥ ህዝብ በመራጨነት ተመዘገበ

ሃዋሳ ጥር 24/2005 በመጪው ሚያዝያ በሚካሄደው የአከባቢና ከተማ አስተዳደር ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ከአምስት ሚሊዮን የሚበልጥ ህዝብ በመራጭነት ተመዝግቦ ካርድ መውሰዱን በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የደቡብ ሕዝቦች ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገለጸ። በደቡብ ክልል በመራጭነት ተመዝግቦ ካርድ ከወሰደው ህዝብ መካከል ከሁለት ነጥብ 4 ሚሊዮን የሚበልጡት ሴቶች ናቸው፡፡ ኃላፊው አቶ አብርሃም ጌዴቦ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በሀገር ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ በሚካሄደው የአከባቢና ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ከታህሳስ 21/2005 እስከ ጥር 21/2005 ድረስ ከአምስት ሚሊዮን የሚበልጥ ህዝብ ተመዝግቧል መራጮቹ ምዝገባውን ያደረጉት በክልሉ 14 ዞኖች 4 ልዩ ወረዳና በ22 የከተማ አስተዳደር በተቋቋሙ 8 ሺህ 130 ምርጫ ጣቢያዎች መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች ከ40 ሺህ ስድስት መቶ የሚበልጡ ምርጫ አስፈፃሚዎች እየሰሩ መሆኑን አስታውቀው በተመሳሳይ ቁጥር የህዝብ ታዛቢዎች ተመርጠው እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ የአከባቢ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲካሄድ በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት አስፈፃሚዎች፣ የሙያ ማህበራት፣ ህብረተሰቡና ሌሎች የባለድርሻ አካላት የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ምርጫ አስፈፃሚዎች በበኩላቸው ጥር 24 እና 25 በሚካሄደው ልዩ ምዝገባ ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ያልተመዘገቡ መራጮች ተመዝግበው ካርድ በመውሰድ ህገ መንግስታዊ መብታቸውን መጠቀም እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=5093&K=1