Posts

Ethiopia: Two Deadlines Gone, Only Five Collect Election Symbols

Legesse Lanikamo, secretary of the Sidama Liberation Movement, says his party decided to participate in the election "after a long discussion with the Sidama people," although he still vows allegiance to the cause of the 33 parties.   On the press conference held at the head office of the Blue party on Tuesday, Asrat Tase, the chairperson of the 33 parties and Gebru Gebremariam, executive member of Medrek, declared that they will be taking their case to the court if the election board does not accept their claim. Only five of the 33 parties that are in dispute with the National Electoral Board of Ethiopia, have collected their candidature symbols for the local election, which may not see the participation of the remaining 28 parties. The five that have joined the list are; the Ethiopian Justice & Democratic Front, Sidama Liberation Movement, Dube & Degeni Nations Democratic Party, Ethiopian Democratic Unity and Yebaher Work Mesmes People D
Image
ከማህበራዊ መረብ ላይ የተገኘ ጽሁፍ   ሲዳማ በደኢህዴን/ኢህአዴግ ዘመን በሲህዴድ አመራር ወቅት የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች   1. የሲዳማ ዞን መስተዳድርና ሲህዴድ የአመራርና የፖለቲካ ስልጣን በእጃቸው በነበረበት ወቅት በርካታ የልማት ስራዎች እንደተጀመሩ ከላይ ተገልጿል፡፡ ከተጀመሩ የልማት ስራዎች መካከል በተለይም የ1ኛና 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ግንባታና በየወረዳውና በየቀበሌው የተስፋፋው መደበኛ ያልሆኑ የት/ ተቋማት፤ በውጭና በሃገር ውስጥ በርካታ የሲዳማ ልጆች የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ እንዲወስዱ የተፈጠሩ ምቹ ሁኔታዎች፣ 2. ጤና ኬላዎች፣ ጤና ጣቢያዎች፣ የቦና ሆስፒታል ግንባታ፣ 3. በሰው ጉልበት የሚሰሩ በርካታ ወረዳዎችን የሚያገናኙ መንገዶች፣ 4. የሲዳማ ልማት ኮርፖሬሽን፣ የሲዳማ ማይክሮ ፋይናንስ፣ በይርጋለም የሚገኘው ፉራ የልማትና ጥናት ምርምር ተቋም፣ የሐዋሳ መሐል ከተማ ጉዱማሌ የገበያ ማዕከላት መመስረትና መገንባት፣ 5. የሲዳማ አስተዳደር አባላትና የልማት መስሪያ ቤት ተወካዮች በአፍሪካ፣ በኤዥያ፣ በአውሮፓና በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በአካደሚክ ትምህርትና በመስክ የስራ ልምድ ጉብኝቶች ሁሉ ለሲዳማ ሕዝብ ልማትና የእድገት ጥማት ምላሽ የሰጡና ተስፋ ሰጪ የልማት ስራዎች ነበሩ፡፡ እነዚህ እንቅስቃሴዎች በዚያው ፍጥነት ቢቀጥሉ ኖሮ ዛሬ የሲዳማ ዞን የት ሊኖር እንደሚችል መገመትም አያዳግትም፡፡   እነዚህና በዝርዝር ያልቀረቡ የልማት ስራዎች የተሰሩት በዋናነት የሲዳማ ዞን መስተዳድር ከአየርላንድ መንግስት ባገኘው የልማት ቀጥተኛ ድጋፍ ሲሆን የመንግሥት ድጎማም እንዳለበት ይታወቃል፡፡ ሲህዴድ ከከሰመ በኋላ በሲዳማ ላይ የተፈጸሙ አሉታዊ ተፅዕኖዎች የደኢህዴን መሰሪ አመራር የድርጅታቸው ዋናው ዓላማና ግብ የሲዳማን ህዝብ መብት

ከሻሸመኔ ጅምላ ንግድ አከፋፋይ ድርጅት /ጅንአድ/ መጋዘን ወጥቶ በህገ ወጥ መንገድ በሀዋሣ ከተማ ሲራገፍ የነበረ ዘይት በቁጥጥር ሥር መዋሉን የክልሉ ንግድ ኢንድስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡

ከሻሸመኔ ጅምላ ንግድ አከፋፋይ ድርጅት /ጅንአድ/ መጋዘን ወጥቶ በህገ ወጥ መንገድ በሀዋሣ ከተማ ሲራገፍ የነበረ ዘይት በቁጥጥር ሥር መዋሉን የክልሉ ንግድ ኢንድስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡ በቢሮው የንግድ ኢንስፔክሽንና ሬጉሌሽን ዋና የሥራ ሂደት  ጊዜያዊ አስተባባሪ ወይዘሮ መስከረም ባህሩ እንደተናገሩት ባለሦስት ሊትር 91 ካርቶንና ባለ አምስት ሊትር 234 ካርቶን ዘይት በአይሱዙ መኪና ተጭኖ በአንድ ነጋዴ መጋዘን ሲራገፍ ከክልሉ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በደረሰ ጥቆማ መሠረት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ በገንዘብ ሲተመን ከ138 ሺህ ብር በላይ የሚያወጣ ሲሆን   ወደ ኦሮሚያ ክልል ጎዴ ዞን የሚሄድ እንደነበር ነው የገለፁት፡፡ በተጠርጣሪው መጋዘን ውስጥ በህገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘ ባለ 2ዐ ሊትር 336 ጀሪካን ዘይትም በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ ተጠርጣሪ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው እንደሆነም አስተባባሪዋ ተናግረዋል፡፡ ባልደረባችን አደገ አየለ እንደዘገበው፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/05TirTextN305.html

በሀዋሳ ከተማ የተጀመረው የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ባለስድስት ፎቅ ህንጻ ግንባታ በመገባደድ ላይ ነው

Image
  አዋሳ ጥር /2005 የኦሞ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም በደቡብ ክልል ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን የብድርና የቁጠባ አገልገሎት ቀልጣፋና ዘመናዊ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ ። ተቋሙ በክልሉ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያስጀመረው የኦውቶሞቲቭ ፕሮጀክት ግንባታ በመፋጠን ላይ መሆኑም ተገልጧል ። የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሙሰማ ጫሊ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ባለፈው አመት በተጀመረው የፕሮጀክት ሀዋሳ ከተማ የሚገኘው የተቋሙን ዋና መስሪያ ቤት በዞን፣ በልዩ ወረዳና በወረዳ ደረጃ ካሉት 172 ቅርንጫፎች ጋር በኮምፒተር ኔት ወርክ የማያያዝ ስራ እየተካሄደ ነው፡፡ በተጨማሪ በሀዋሳ ከተማ የተጀመረው የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት ባለስድስት ፎቅ ህንጻ ግንባታ በመገባደድ ላይ እንደሚገኝና በሚቀጥለው ወር ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ አስረድተዋል፡፡ በክልሉ የ12 ቅርንጫፎች ባለሁለት ፎቅ ህንጻ ግንባታ በቅርቡ መጀመሩንና በ119 ንዑስ ቅርንጫፎች ከተጀመረው የቢሮ ግንባታ ውስጥም እስካሁን የ40ዎቹ ስራ ሲጠናቀቅ የቀሪዎቹ እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ይከናወናል ብለዋል ። በየደረጃው ያሉት ሁሉም ቅርንጫፎ ቢሮዎችን በማሻሻል በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ የታገዘ የኮምፒተር ኔት

በሲዳማ ዞን በዘንድሮዉ የበጋ ወራት ከ38 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በመስኖ እየለማ ነው፡፡

አዋሳ ጥር 2005 በደቡብ ክልል ሲዳማ ዞን በዘንድሮዉ የበጋ ወራት ከ38 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት ላይ የተለያዩ ሰብሎችና አትክልትና ፍራፍሬ እየለማ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ ። በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች በመስኖ እየለማ ካለዉ መሬት ከስድስት ሚልዮን ኩንታል የሚበልጥ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጧል ። በመምሪያ የመስኖ ልማትና ተቋማት አስተዳደር ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ሙሉጌታ ማሞ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በሁለት ዙር በሚካሄደዉ የበጋ መስኖ ልማት ከ530 ሺህ የሚበልጡ አርሶ አደሮች እየተሳተፉ ነዉ ። የመስኖ ልማቱ እየተካሄደ ያለዉ በየአካባቢው የሚገኙ ምንጮችን በማጎልበት፣ አነስተኛ ጉድጓዶችን በመቆፈር፣ ወንዞችን በመጥለፍና በቤተሰብ ደረጃ የኩሬ ውሃ በማሰባሰብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች እየተካሄደ ባለዉ የመስኖ ልማት እስካሁን ከ12ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአትክልትና ፍራፍሬ ፣በስራስርና በስራ ስርና በሌሎች ቋሚ ሰብሎች ተሸፍኗል ። ቀደም ሲል አብዛኛው የዞኑ አርሶ አደሮች የዝናብ ወቅትን ጠብቀዉ በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ በማምረት የድካማቸዉ ተጠቃሚ ሳይሆኑ መቆየታቸዉን አመልክተዉ በአሁኑ ጊዜ በዓመት ከሁለት ጊዜ በላይ በማምረት ኑሯቸዉን ማሻሻል ጀምረዋል ። በመልጋ ወረዳ፣ የጉጉማ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደሮች አቡሌ ክፍሌ እና መላኩ አበጀ ከሶስት ዓመታት በፊት እጅግ አስቸጋሪ የኑሮ ደረጃ ላይ እንደነበሩ አስታውሰዉ ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ በመጠቀም የመስኖ ልማት ከጀመሩ ወዲህ ኑሮአቸው እየተለወጠ ከመምጣቱም ባሻገር እስከ አገር አቀፍ ድረስ ሞዴል አርሶ አደር በመሆን ለሽልማት መብቃታቸውን ገልጸዋል፡፡