Posts

ለክብራን የሲዳማወራንቻ ብሎግ ኣንባቢያን በሙሉ

Image
ክብራን የሲዳማወራንቻ ብሎግ ኣንባቢያን ለኣንድ ወር ያህል ስራ ያቆምን መሆናችንን እና ከኣንድ ወር በኃላ በኣዳዲስ ዝግጅቶች የምንመለስ መሆናችንን እናስታውቃለን። እናመሰግናለን መልካም የገና በዓል !

የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ (ሲኣን) ኣዲሱ ኣመራር የሲኣንን የቀድሞ ዝና ለመመለስ እና የሲዳማ ህዝብ ፖለቲካዊ መብት መከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ እንደምታገል ኣስታወቀ ፤ በቅርቡ ለምካሄደው የኣከባቢ ምርጫ ከፍተኛ ዝግጅት በማድረግ ላይ ነው።

Image
የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ (ሲኣን) ኣዲሱ ኣመራር የሲኣንን የቀድሞ ዝና ለመመለስ እና የሲዳማ ህዝብ ፖለቲካዊ መብት መከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ እንደምታገል ኣስታወቀ ፤ በቅርቡ ለምካሄደው የኣከባቢ ምርጫ ከፍተኛ ዝግጅት በማድረግ ላይ ነው። ዝርዝሩን በምከተለው ሊንክ ያዳምጡ:: ለድምጽ ጥራት ማነስ ይቅርታ እንጠይቃለን!   ሲዳማ ተናገር የሬዲዮ ፕሮግራም

የሲዳማ ወጣቶች ንቅናቄ መግለጫ

Statement to Sidama youth movement On 2009, as we all know, the children of Sidama massacred by the current prime Minister of Ethiopia Haile Mariam Desalgn, at Awassa, Loque vicinity, Sidama state and the whole sidama population response to a massacre unprecedented in its nature and scale. On the occasion of the tenth anniversary of that uprising, the youth and students, the children, parents, teachers and other professionals; the workers in town, in commerce, industry and the farms; the religious community - in fact, the entire oppressed population together bound together by the blood that covered the streets of Awassa, the blood that has since soaked the soil of our motherland in even bigger quantities. On this truly historic occasion the nation will pay fitting tribute to the young heroes and martyrs. And so the repression we experience today is not new. But as we can see today the sacrifices of those heroes and martyrs were not in vain. The declaration of eviction of Sid

በሴቶች የፕሪምየር ሊግ ውድድር ሲዳማ ቡና ሩብ ፍፃሜ ገባ

Image
ሰኞ, 24 ታህሳስ 2012 11:05 በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መለስ ዋንጫ የሴቶች ውድድር ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ደደቢትና ሲዳማ ቡና ከየምድባቸው በበላይነት አጠናቀዋል። የምስራቅ ዞን ምድብ አሁንም መጨረሻው አልታወቀም።   ህዳር 29/2005 የተጀመረው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የሴቶች ውድድር ሶስተኛ ሳምንት ቅዳሜና እሁድ ማለትም ታህሳስ 13 እና 14/2005 ቀጥሎ ተካሂዷል። በቅዳሜው ጨዋታ የማእከላዊ ዞን ምድብ አንድ ሁለት ጨዋታዎች ተከናውነዋል። በዚህም ደደቢት ኢትዮጵያ ቡናን 3 ለ 0 በመርታት ምድቡን በዘጠኝ ነጥብ 1ኛ ሆኖ ያጠናቀቀበትን ውጤት ይዞ ወጥቷል። መብራት ሃይልን 3 ለ 1 የረታው ኢትዮጵያ መድህንም በ6 ነጥብ ሁለተኛ ሆኖ ሩበ ፍፃሜ መግባቱን አረጋግጧል። ኢትዮጵያ ቡናና መብራት ሃይል ከምድቡ ሳያልፉ ቀርተዋል። ቀሪ 4 ጨዋታዎች ደግሞ እሁድ ተከናውነዋል። በማዕከላዊ ዞን የምድብ ሁለት ጨዋታዎች በአዲስ አበባ ስታድየም ሲከናወኑ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኢትዮጵያ ውሃ ስራዎች ላይ ከደርዘን በላይ ግቦችን አስቆጥሯል። ንግድ ባንክ 14 ለ 0 የረታበት ጨዋታ በዘንድሮው ውድድር ከፍተኛ ግብ የተቆጠረበት ጨዋታ ሆኖ አልፏል። ከ14ቱ ግቦች ሽታዬ ሲሳይ በግሏ 7ቱን ግቦች ከመረብ ስታገናኝ፣ ረሂማ ዘርጋ 5ቱን በስሟ አስመዝግባለች። የሽታዬ ሲሳይ እህት የሆነችው ብዙነሽ ሲሳይ ደግሞ ቀሪዎቹን ሁለት ግቦች አስቆጥራለች። በዚህም መሠረት ሶስቱንም ጨዋታዎች በአሸናፊነት የተወጣው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምድቡን በበላይነት አጠናቋል። በዚሁ ምድብ እኩል የማለፍ እድል ይዘው ወደ ሜዳ የገቡት መከላከያና የቅ/ጊዮርጊስ 1 ለ 1 ተለያይተዋል። ሁለቱም 4 ነጥቦችን በመያዝ መከላከያ የተሻለ የግብ ክፍያ ስላለው ንግድ ባንክን ተከትሎ ግማሽ

የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኪሚቴ መደበኛ ስብሰባ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በማሳተላለፍ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ ታሀሳስ 14/2005 የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኪሚቴ መደበኛ ስብሰባ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በማሳተላለፍ ተጠናቀቀ፡፡ የግንባሩ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጸው የፌዴራል መንግስት ተቋማትን የ2005 የዕቅድ ዝግጅት ምዕራፍና ዋና ዋና የመንግሥትና የድርጅት ሥራዎችን በማስቀደም ነው የሁለት ቀናት ስብሰባውን የጀመረው፡፡ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ከ2004 አፈጻጸም ግምገማ ከተለዩት ደካማና ጠንካራ የአፈጻጸም ውጤቶች በመነሳት የተካሄደውን የዕቅድ ዝግጅትና ፈፃሚ የማዘጋጀት ሂደት ፈትሿል፡፡ በዝግጅት ምዕራፍ ፈጻሚ የማዘጋጀት ሂደት ሦስቱንም የልማት ኃይሎች ማለትም የድርጅትን፣ የመንግስትንና ዋናው ፈጻሚና ተጠቃሚ የሆነውን የሕዝብ አቅም በዝርዝር ለይቶ ለመገንባት የተደረገው ጥረት ከወትሮው የተሻለ አፈጻጸም የታየበት እንደሆነ አረጋግጧል፡፡ በተለይም በእያንዳንዱ ዘርፍ ከተልዕኮው አንጻር ተጠቃሚ ወይም ተገልጋይ የሆነውን የሕዝብ ወገን በዝርዝር ለይቶ ቀጣይነት ያለውና በተጠያቂነት ላይ የተመሰረተ የተሳትፎና የግንኙነት ሥርዓት ለመገንባት የተጀመረው ጥረት መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና የመንግስትን አገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍና ለማረጋገጥ የሚያስችል በመሆኑ በእስካሁኑ የተሻለ ርቀት ከሄዱት ዘርፎች ልምድ በመነሳት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በአጽንኦት አሳሰቧል፡፡ በዝግጅት ሥራው ተመስርቶ በየዘርፉ የተከናወኑትን አባይት የልማት ሥራዎችን የፈተሸው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ፈጣኑ የኢኮኖሚ ዕድገት ይበልጥ ጤንነቱን ጠብቆ በመቀጠል ላይ መሆኑን ገምግሟል፡፡ የከተማውን ነዋሪ በተለይም አነስተኛ ገቢ ያለውን የህብረተሰብ ክፍል በመፈታተን ላይ የነበረው የዋጋ ግሽበት ቀደም ሲል ከ39 በመቶ በላ