Posts

የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኪሚቴ መደበኛ ስብሰባ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በማሳተላለፍ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ ታሀሳስ 14/2005 የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኪሚቴ መደበኛ ስብሰባ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በማሳተላለፍ ተጠናቀቀ፡፡ የግንባሩ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጸው የፌዴራል መንግስት ተቋማትን የ2005 የዕቅድ ዝግጅት ምዕራፍና ዋና ዋና የመንግሥትና የድርጅት ሥራዎችን በማስቀደም ነው የሁለት ቀናት ስብሰባውን የጀመረው፡፡ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ከ2004 አፈጻጸም ግምገማ ከተለዩት ደካማና ጠንካራ የአፈጻጸም ውጤቶች በመነሳት የተካሄደውን የዕቅድ ዝግጅትና ፈፃሚ የማዘጋጀት ሂደት ፈትሿል፡፡ በዝግጅት ምዕራፍ ፈጻሚ የማዘጋጀት ሂደት ሦስቱንም የልማት ኃይሎች ማለትም የድርጅትን፣ የመንግስትንና ዋናው ፈጻሚና ተጠቃሚ የሆነውን የሕዝብ አቅም በዝርዝር ለይቶ ለመገንባት የተደረገው ጥረት ከወትሮው የተሻለ አፈጻጸም የታየበት እንደሆነ አረጋግጧል፡፡ በተለይም በእያንዳንዱ ዘርፍ ከተልዕኮው አንጻር ተጠቃሚ ወይም ተገልጋይ የሆነውን የሕዝብ ወገን በዝርዝር ለይቶ ቀጣይነት ያለውና በተጠያቂነት ላይ የተመሰረተ የተሳትፎና የግንኙነት ሥርዓት ለመገንባት የተጀመረው ጥረት መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና የመንግስትን አገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍና ለማረጋገጥ የሚያስችል በመሆኑ በእስካሁኑ የተሻለ ርቀት ከሄዱት ዘርፎች ልምድ በመነሳት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በአጽንኦት አሳሰቧል፡፡ በዝግጅት ሥራው ተመስርቶ በየዘርፉ የተከናወኑትን አባይት የልማት ሥራዎችን የፈተሸው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ፈጣኑ የኢኮኖሚ ዕድገት ይበልጥ ጤንነቱን ጠብቆ በመቀጠል ላይ መሆኑን ገምግሟል፡፡ የከተማውን ነዋሪ በተለይም አነስተኛ ገቢ ያለውን የህብረተሰብ ክፍል በመፈታተን ላይ የነበረው የዋጋ ግሽበት ቀደም ሲል ከ39 በመቶ በላ

“ገዥውን ፓርቲ የሚጠቅሙ እየመሰላቸው በምርጫ ወቅት ችግር የሚፈጥሩ አስፈጻሚዎች አሉ”

Image
አቶ አስመላሽ ወልደ ሥላሴ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ የፍትሕና የአስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከአራት ወራት በኋላ ሚያዝያ 6 እና 13 ቀን 2005 ዓ.ም. በመላ አገሪቱ የአካባቢና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ይካሄዳል፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን ግልጽና ተዓማኒ ለማድረግ ደፋ ቀና ማለት ጀመርኩ ካለ ሰነባብቷል፡፡ ባስቀመጠው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት የምርጫ ቁሳቁሶችን ከማሳተም፣ ከማዘጋጀትና ከማሠራጨት ጐን ለጐን ደግሞ፣ ቀደም ብሎ ማከናወን ቢገባውም በምርጫው ዙሪያ ውይይትና ሥልጠና በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ቦርዱ እያደረጋቸው ከሚገኙት የምርጫ ክንውኖች መካከል ታህሳስ 7 እና 8 ቀን 2005 ዓ.ም. በአዳማ ከተማ ኤክስኪዩቲቭ ሆቴል ለጋዜጠኞች የሰጠው የሁለት ቀናት ሥልጠና ተጠቃሽ ነው፡፡ ሥልጠናውን የሰጡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙዩኒኬሽን መምህር ዶክተር ገብረ መድኅን ስምዖንና በተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ የፍትሕና የአስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አስመላሽ ወልደ ሥላሴ ናቸው፡፡ አቶ አስመላሽ “የኢትዮጵያ የምርጫ ሕግና አፈጻጸሙ” በሚል ርዕስ ባዘጋጁት ጥናታዊ ጽሑፍ ዙሪያ የምርጫ ቦርድ አባላትንና ሌሎች የምርጫ ክንውኖችን በሚመለከት ከሥልጠናው ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች ቀርበውላቸው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ አቶ አስመላሸ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች የሰጡትን ምላሽ ታምሩ ጽጌ እንደሚከተለው አዘጋጅቶታል፡፡ ጥያቄ፡- የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ አባላት ገለልተኛ ናቸው ብለው ያምናሉ? አቶ አስመላሽ ፡- የምርጫ ቦርድ አባላት ገለልተኛ ናቸው ወይስ አይደሉም ለማለት ዋናውና አንዱ መሠረታዊ ጉዳይ፣ የሚለዩበትን መሠረታዊ ነገር መፈተሽ ነው፡፡ የምርጫ ቦርድ አ

የሕወሓት አብዮት ሰለባዎች.. የአዋሳ ከንቲባ አቶ ሽብቁ እስር ተፈረደባቸው

የሕወሓት አብዮት ሰለባዎች.. የአዋሳ ከንቲባ እስር ተፈረደባቸው   ከሰሞኑ በደቡብ ክልል ጉራ ፈረዳ ወረዳ የአማራ ክልል ተወላጆች ተባረው መሬታቸው ለሌሎች የስርዓቱ ደጋፊዎችና አባላት በሃራጅ መሸጡን ዘ-ሐበሻ ስትዘግብ ቆይታ ነበር። ከአዲስ አበባ የመንግስት ሚዲያዎች ያስተላለፉት ዜና ደግሞ የሃዋሳ ከተማ ነዋሪ ላልሆኑ ሰዎች መሬት የሸጡ የክልሉ ባለስልጣናት በሙስና ወንጀል ተከሰው እንደተፈረደባቸው ያትታሉ። የሕወሓት/ኢሕአዴግ ሥር ዓት አብዮት ለስልጣኑ ታማኝ ያልሆኑትን በሙስና ሰብብ ሲበላ መቆየቱን ያስታወሱት አስተያየት ሰጪዎች በታምራት ላይኔ ጀምሮ በስዬ አብርሃ ለጥቆ አሁን የጸረ ሙስና ሕጉ የቂም በቀል መወጣጫ ሆኗል ሲሉ ይተቻሉ። ኃላፊ በነበሩበት ወቅት ስልጣናቸውን አላግባብ በመጠቀም መሬት ለግለሰቦችና ድርጅቶች ሰጥተዋል በሚል የሙስና ወንጀል ተከሰው የነበሩ የቀድሞ የሃዋሳ ከተማ ከንቲባና ሌሎች ስድስት ተከሳሾች በእስራትና በገንዘብ መቀጣታቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን እያዳነቁ ዘግበዋል።  በማዳነቂያ ዜናቸው ላይ “ግለሰቦቹ ለመኖሪያ ቤት የማይፈቀድን ቦታ ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ፥ የተጻፈውን ዕገዳ በመጣስ የተለያዩ ግለሰቦች እና ጋዜጠኞችን ጨምሮ በሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ላልሆኑ ስምንት ሰዎች መሬትበመስጠታቸው ነው የተከሰሱት (የተሰመረበትን ይመልከቱ)ሲሉ ነው የመንግስት ሚድያዎች የዘገቡት። እነዚሁ ሚዲያዎች ዘገባቸውን ሲያጥናቅር “የደቡብ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የነበሩትን ፥ አቶ ሽብቁ ማጋኔን ጨምሮ 6 ተከሳሾች ላይ ከአንድ እስከ ስምንት ዓመት በሚደርስ እስራትና ከ2 እስከ 20 ሺህ ብር እንዲቀጡ፤ ፍርድ ቤቱ የክልሉ ጸረ ሙስና ኮሚሽን ይግባኝ በጠየቀባቸው ፥ አቶ ሽብቁ ማጋኔ፣ አቶ እንድርያስ ፉ

በሃዋሳ ከተማ ስልጣንን ተገን በማድረግ ወንጀል የፈጸሙ የስራ ሃላፊዎች በእስራትና ገንዘብ ተቀጡ

አዋሳ ታህሳስ 12/2005 የሀዋሳ ከተማ ከንቲባና ማዘጋጃ ቤት ኃላፊ በነበሩበት ወቅት ስልጣናቸውን አለአግባብ በመጠቀም መሬት ለግለሰቦችና ድርጅቶች ሰጥተዋል በሚል የሙስና ወንጀል ተከሰው የነበሩ የከተማው ከንቲባና ሌሎች ስድስት ተከሳሾች በእስራትና ገንዘብ እንዲቀጡ ተወሰነ። የደቡብ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ባስቻለው ችሎት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የነበረውን ሽብቁ ማጋኔን ጨምሮ 6 ተከሳሾች ላይ ከስምንት ዓመት እስከ አንድ ዓመት በሚደርስ እስራትና ከ20ሺህ እስከ 2 ሺህ ብር እንዲቀጡ ወስኗል። ፍርድ ቤቱ የክልሉ ጸረሙስና ኮሚሽን ይግባኝ በጠየቀባቸው ሽብቁ ማጋኔ፣ እንድርያስ ፉላሳ፣ ጸጋዬ አረጋ፣ ጉደታ ጉምቤ፣ አስራት ግቻሞና ከበደ ካያሞ ላይ የእስራትና ገንዘብ ቅጣቱን የወሰነው የስር ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ውሳኔ በመሻር ነው። ግለሰቦቹ ለባለኮከብ ሆቴሎችና ከፍተኛ ኢንቨስትመንቶች ካልሆነ በቀር የመኖሪያ ቤት ቦታ መስጠት እንደማይቻል ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር የተጻፈውን ዕገዳ በመጣስ ለግለሰቦች እንዲሁም ጋዜጠኞችን ጨምሮ በሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ላልሆኑ ስምንት ሰዎች መሬት በመስጠታቸው ቅጣቱ ተጥሎባቸዋል ብሏል። በዚሁ መሰረት የሀዋሳ ከተማ የነበረው ሽብቁ ማጋኔ ላይ የአምስት አመት ከስድስት ወር ጽኑ እስራትና የአምስት ሺህ ብር የገንዘብ መቀጫ ተጥሎበታል። የሃዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት የመሬት ልማትና አስተዳደር የስራ ሂደት ባለቤት የነበረው እንድሪያስ ፉላሳና በማዘጋጃ ቤቱ የመሬት ልማትና አስተዳደር የስራ ሂደት ባለሙያ የነበረው ጉደታ ጉምቤ እያንዳንዳቸው በ5 ዓመት ከ6 ወር እስራትና በ15 ሺህ ብር እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል። የታቦር ክፍለ ከተማ ማዘጋጃ ቤት የመሬት ልማትና አስተዳደር ስራ ሂደት አስተባባሪ በነበረው አስራት ግቻ

በሀዋሳ ከተማ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመስማራት ከሃገር ውስጥም ሆነ ከውጪ የሚመጡ ባሀብቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የከተማው አስተደደር አስታወቀ፡፡

Image
ባለፉት አራት አመታት በከተማው በባለሀብቶች በተከናወኑ የኢንቨስትመንት ስራዎች ከ23ሺህ በላይ ነዋሪዎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸዋል፡፡ በሌላም በኩል የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደው ወደ ስራ ያልገቡ ባለሃብቶች በአጭር ጊዜ ወደ ስራ እንዲገቡ የከተማ አስተዳደሩ አሳስቧል፡፡ የሀዋሳ ከተማ በሃገር አቀፍ ደረጃ ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ካሉ ከተሞች በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ ሲሆን ለዚህም እንደምክንያት የሚነሳው ለንግድ እንቅስቃሴ የምትመች መሆኑና የሃይቅዳር ከተማ መሆኗ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ከተማዋን የቱሪስት መዳረሻ፣ የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ በተያዘው አመት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ አቶ ዮናስ ዮሴፍ ገልፀዋል፡፡ በተለይ ይህን ስራ የበለጠ ማስኬድ እንዲቻል ከተማውን የማስተዋወቅ ስራ ትኩረት እንደተሰጠው አመልክተዋል፡፡ 4ኛው የከተሞች ሳምንት ተካሂዶ  ሃዋሳ ሁለት ዋንጫ በማግኘት አሸንፋ ከተመለሰች በሁዋላ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ለመሰማራት ከሃገር ውስጥም ሆነ ከውጭ በርካታ ባለሃብቶች ጥያቄ እያቀረቡ እንዳለ አቶ ዮናስ ገልፀዋል፡፡ በዚህም የከተማ አስተዳደሩ የተሻሉ አሰራሮችን በመዘርጋት ባለሀብቶችን ለማስተናገድ መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡ በከተማዋ ባለፋት አራት አመታት ውስጥ ኢንቨስት ባደረጉ ባለሃብቶች ከ 23 ሺህ በላይ የከተማዋ ነዋሪዎች የስራ እድል ተጠቃሚ መሆናቸውንና ኢንቨስትመንት ይበልጥ በከተማዋ ለማስፋፋት ዘመናዊ ድረ ገጽ በመክፈት የማስተዋወቅ ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል፡፡ በሌላ በኩል በተለያዩ ወቅቶች የኢንቨስትመንት ቦታ ወስደው ያላለሙ ባለሃብቶች እንዳሉ አረጋግጠናል ያሉት አቶ ዮናስ፣ 60 ባለሀብቶችን አሰተዳደሩ ወደ ልማት እንዲገቡ ማወያየቱንና ከስምምነት ላ