Posts

በሀዋሳ ከተማ ከ253 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የልማት ፕሮግራም እየተካሄደ ነው

Image
ሃዋሳ ታህሳስ 04/2005 በሀዋሳ ከተማ መንግስታዊ ያልሆኑ 74 ድርጅቶች ከ253 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ በጀት ህብረተሰቡን ያሳተፉ የልማት ፕሮግራሞች እያካሄዱ መሆናቸውን የከተማው ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ ገለጸ፡፡ የመምሪያው ምክትል ሃላፊ አቶ አሻሬ ኡጋ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በከተማው ስምንት ክፍለ ከተሞች የሚካሄደው የልማት ፕሮግራም ለሚቀጥሉት ሶስት አመታት የሚቆዩ ናቸው፡፡ ከልማት ፕሮግራሞቹ መካከል የጤና፣ የትምህርት፣ የከተማ ግብርና፣ የአካባቢ ጥበቃ፣ የህጻናት ድጋፍና ክብካቤ፣የገቢ ማስገኛ ፣አቅም ግንባታን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸው ዘርፎች መሆናቸውን አስታውቀዋል የከተማውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ለማፋጠን መንግስት የሚያደረገውን ጥረት ለማገዝ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ህብረተሰቡን በማሳተፍ የሚካሄዱት የልማት ፕሮግራሞች ሲጠናቀቁ ከ200ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ገልጸዋል፡፡ የድርጅቶቹን የስራ አንቅስቃሴና አፈጻጸም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ክትትልና ቁጥጥር እያደረጉ መሆናቸውንም አመልከተዋል፡፡ እየተጠናቀቀ ባለው የአውሮፓውያኑ 2012 የስራ ዘመን ድርጅቶቹ በመደቡት ከ84 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የከተማው ነዋሪዎች ተጠቃሚ ያደረጉ ተመሳሳይ የልማት ፕሮግራሞች ማካሄዳቸውን የመምሪያው ምክትል ሃላፊ ገልጸዋል፡፡ http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=3941&K=1

ስራ ኣጥነት እና የወጣቶች እሮሮ በሲዳማ

Image
  በኪንክኖ ኪአ በሲዳማ ዞን በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች በሥራ አጥነት የሚሰቃዩ ወጣቶች ቁጥር ከጊዜ ቀደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱ ተገለጸ፡፡ ሥራ ያጡ ወጣቶችም በተለያዩ ወረዳዎች ሠላማዊ ሠልፍና ተቃዉሞ እያሰሙ መሆናቸዉ ታዉቀዋል፡፡ ሰሞኑን በአርቤጎና ወረዳ በተካሄደዉ ተቃዉሞ ሰልፍ ሳቢያም ከ15 በላይ ወጣቶች መተሰራቸዉ ተሰመቶአል፡ በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ ሙያና ት/ት ዘርፎች ተከታትለዉ ከተመረቁ በኀላ የሥራ እድል በማጣት በርካታ ወጣቶች በከፍተኛ ችግር ላይ መዉደቃቸዉ በሰፊዉ ይነገራል፡፡ የከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ት/ት ካጠናቀቁ በኀላ በተለያዩ ኮሌጆች፡ የሙያ ማሠልጠኛ ተቐማትና ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸዉን የተከታተሉ ወጣቶች ቁጥር በርከት እያሌ መምጣቱ የሚነገር ሲሆን ከዚሁ ቁጥር ጋር የሚመጣጠን የሥራ እድል በመንግሥት ባለመመቻቸቱ ከፍተኛ የሆነ የሥራ አጥነት ችግር በዞኑ ተንሰራፍተዋል፡፡     ወጣቶቹ በት/ት የቀሰሙትን እዉቀት ተጠቅመዉ ሕብረተሰቡን ለማገልገልና የራሳቸዉን ሕይወት ለማሻሻል ከፍተኛ ተነሳሽነትና አቅምያላቸዉ ቢሆንም ት/ታቸዉን አጠናቀዉ ከ5 እና ከዚያ በላይ ዓመታትን የለሥራ በማሳለፋቸዉ ሰቢያ ሊለማ የሚችል እዉቀት፤አቅምና ጉልበት በጥቅም ላይ ሣይዉል እንደሚባክን ተጠቁመዋል፡፡   የሥራ አጥ ወጣቶች የኑሮ መሠረት በአጭሩ አብዛኞቹ የሥራ አጥ ወጣት ምሁራን የተገኙት ከገጠሩ ማህበረሰባችን ከፍል ነዉ፡፡ ትምህርታቸዉን ለመከታተልም ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ወጪ አድርገዉ፤ አብዛኞቹ ደግሞ በግል ት/ት ተቐማት በራሳቸዉ አቅም ትምህርታቸዉን የተከታተሉ ናቸዉ፡፡ እንደሚታወቀዉ አብዛኛዉ የሲዳማ ማህበረሰብ የገጠር ነዋሪ በመሆኑ የኢኮኖሚ መሠረቱ ግብርና ከመሆኑም በተጨማሪ የገቢ ምንጫቸዉና አቅምቸዉ ይኼ ነዉ የሚባል አይደለም፡፡ ይህም ሆኖ እነ

የሀዋሳን መስህቦች ከጎበኙ ቱሪስቶች ከ16 ነጥብ 8ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኘ፡፡

Image
አዋሳ ታህሳስ 3/2005 በሀዋሳ ከተማና አካባቢውን የሚገኙ የመስህብ ቦታዎችን ባለፉት ሶስት ወራት ከጐበኙ የሀገር ውስጥና የውጪ ቱሪስቶች ከ16 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የከተማው አስተዳደር ባህል፣ ቱሪዝምና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳይ መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የቱሪዝምና ፓርኮች የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ አዲሴ አኔቶ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በሀዋሳ ከተማና አካባቢው የሚገኙ የመስህብ ቦታዎች ባለፉት ሦስት ወራት በ47 ሺህ 728 የሀገር ውስጥና 10 ሺህ 139 የውጪ አገር ቱሪስቶች ተጐብኝተዋል፡፡ ቱሪስቶቹ የጎበኟቸው የመስህብ ቦታዎች የሀዋሳ ሀይቅንና በውስጡ ያሉት ብርቅዬ የአእዋፍ ዝርያዎች፣ ጉማሬዎች ፣ በከተማው ዙሪያ የሚገኙት የአላሙራና የታቦር ተራራዎች፣ የጥቁር ውሃ ደን ፣ የቡርቂቲ ፍል ውሃ ፣ የሲዳማ ባህላዊ ጎጆዎችንና የተለያዩ ብሄረሰቦች የባህል አልባሳት ፣ አመጋገብና የሙዚቃ መሳሪዎች ጨምሮ ሌሎች ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊና ታሪካዊ ቅርሶች ነው፡፡ የተገኘው ገቢም ሆነ የቱሪስቶች ቁጥር ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር አምስት በመቶ ብልጫ እንዳለው ገልፀዋል፡፡ ገቢውም ሆነ የቱሪስቶች ቁጥር ሊጨምር የቻለው የቱሪዝም ሀብቱን በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በማስተዋወቅ ጎብኚዎችን ለመሳብ በተደረገው ጥረት መሆኑን የስራ ሂደቱ አስተባባሪ አመልከተዋል፡፡ የሀዋሳ ከተማ የአየር ንብረት ተሳማሚነት፣ የመስተንግዶና የመሰረተ ልማት መስፋፋትን ጨምሮ ለመዝናናትና ለኑሮ ባለው ምቹነት አካበቢውን ለመጎብኘት የሚመጡ የሀገር ውስጥና የውጪ ቱሪስቶች ቁጥር በየአመቱ እየጨመረ እንዲሄድ አስተዋጽኦ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡ የጐብኝዎች ቁጥር መጨመርን ተከትሎም የሚገኘው ገቢ በዚያው መጠን እያደገ መሆኑን አስተባበሪው

የነጭ ሪቫን ቀን በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ

Image
አዋሳ ታሀሳሰ 03/2005 የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ መምህራን፣ ተማሪዎችና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ፆታዊ ጥቃቶችን ለማስቆም የተቀናጀ ጥረት እንደሚያደርጉ አስታወቁ፡፡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ከዩኒቨርስቲ ጋር በመቀናጀት ያዘጋጀው አለም አቀፍ የነጭ ሪቫን ቀን ትናንት በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል፡፡ ቀኑን አስመልክቶ በዩኒቨስርቲው በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ እንደተገለፀው በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ፆታዊ ጥቃቶችን ማሰቆም ሰብአዊ መብቶች በማስተባበር ልማትና እድገትን ለማፋጠን ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው፡፡ የዩኒቨርስቲው ሶስቱም ካምፓስ መምህራን፣ ተማሪዎችና የአስተዳደር ሰራተኞች በውይይቱ መጨረሻ በተቋሙ ውስጥም ሆነ ውጭ በሴቶች ላይ የሚፈፀመውን ማንኛውንም ጥቃት እና ትንኮሳዎችን ለመከላከል ግንዛቤ በመፍጠር የበለጠ ትኩረት ሰጥተው እንደሚንቀሳቀሱ ተናግረዋል፡፡ በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ የሃይል ጥቃቶች የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በመሆናቸው ከተለያዩ ማህበራት፣ መንግስታዊ ከሆነ ተቋማትና ከተለያዩ የባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ችግሩን ለመግታት ግንባር ቀደም ሚና ለመጫወት ዝግጁ መሆናቸውንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የስርዓተ ፆታ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወይዘሮ በዛ ነገዎ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት መንግስት የብሄር ብሄረሰቦች መብትና ጥቅም ከማስጠበቅ ባሻገር የሴቶችን አኩልነት ፣ የሃይማኖት ነፃነትን ያረጋገጠ በመሆኑ ሁሉም ተገንዝቦ ተግባራዊ ማድረግ ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ኮሚሽነር አቶ አስማሩ በሪሁን በበኩላቸው ፆታዊ ጥቃትና ትንኮሳዎች ሴቶች ለሀገር ልማትና እድገት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ የሚገድብ፣ በትምህርት ላይ ያላቸውን ተሳትፎ የሚያቀጭጭ፣ የሀገሪቱ የ

ሹመት ችግር ካልፈታ ፋይዳ ቢስ ነው!

ሰላም! ሰላም! ለዛና ጨዋታ ናፈቀን አይደል ጎበዝ? የድርቅ ታሪካችንን ለማጥፋት ስንረባረብ ሳይታወቀን የጨዋታ ድርቅ እየወረሰን መጣ መሰለኝ። የሚወራው፣ የሚሰማው፣ የሚዘፈነው፣ የሚታየው ሁሉ ለዛ በማጣት ድርቅ ከተመታ ምን ይውጠናል? እንዴ መኖር እየጠላን እንዴት እንዘልቃለን? እውነት እውነት ስላችሁ! ሳቅና ጨዋታ ከአታካቹ ኑሯችን ከተባረረ መሀል ላይ ስንዋልል ጥሩ አይመስለኝም። ‹‹አይ አንተ ሁሌም አንድ ሐሳብ አያጣህም?›› አለችኝ ውዷ ባለቤቴ ማንጠግቦሽ፣ ‹‹ሳቅ አላማረሽም?›› ብዬ ብጠይቃት። በነገራችን ላይ ማንጠግቦሽ ከት ብላ ከሳቀች ድንበር ተሻጋሪ ድምጿን ማንም ነው ሚሰማው። አሁን ታዲያ በገባሁ በወጣሁ ቁጥር ‹‹ምነው ሰላም አይደላችሁም?›› የሚለኝ ሠፈርተኛ በዝቷል።  ይኼኔማ አንዳንዱ ተጣሉም ብሎ ያስወራ ይሆናል። ሰው እንዴት የሰውን ጓዳ ጎድጓዳ እየተከታተለ እንደሚኖር ሳስብ በእጅጉ ይደንቀኝ ጀመር። በነገራችን ላይ ከመሬት እየተነሳ ባለፀጋ የሚሆነው አልበዛባችሁም? መጠቃቀም በሕዝብ ሀብት ባይሆን ጥሩ ነው እያልን ብንመክር ብናስመክር ማን ከመጤፍ ቆጠረን? ‹‹ምርጫ ሲደርስ ብቻ የሚቆጠረው ድምፃችን ከወዲሁ ሰሚ ቢያገኝ ኖሮ የሌባው ቁጥር እንዲህ ባልበዛ ነበር፤›› ይለኛል የባሻዬ ልጅ በአንድ ጀንበር የሚከብሩ ሲበዙበት። መክበራቸው ሳያንስ ተፈርተው መኖራቸው የሚያበሳጨን አደባባይ ይቁጠረን። እናም ሳቅ ጠፋ የምለው በየትኛውም ሥፍራ እያረሩ መሳቅ የደስታ ምልክት ነው ተብሎ ስለማይቆጠር ነው።  ለነገሩ ዝም ብላችሁ ብትታዘቡ እንኳን መሳቅ ይቅርና እሪ ብሎ ማልቀስስ ተወዷል። (ቆይ የማይወደደው ምን ይሆን?) ‹‹ይኼ ለብ ማለት ደግ አይደለም አንበርብር፤›› ይሉኛል ባሻዬ ጋቢያቸውን እያጣፉ። ኑሯችን ከአንዱ ወደ አንዱ እንደኳስ እየጠለዘ ሲጫወትብን መሳቅ