Posts

ሹመት ችግር ካልፈታ ፋይዳ ቢስ ነው!

ሰላም! ሰላም! ለዛና ጨዋታ ናፈቀን አይደል ጎበዝ? የድርቅ ታሪካችንን ለማጥፋት ስንረባረብ ሳይታወቀን የጨዋታ ድርቅ እየወረሰን መጣ መሰለኝ። የሚወራው፣ የሚሰማው፣ የሚዘፈነው፣ የሚታየው ሁሉ ለዛ በማጣት ድርቅ ከተመታ ምን ይውጠናል? እንዴ መኖር እየጠላን እንዴት እንዘልቃለን? እውነት እውነት ስላችሁ! ሳቅና ጨዋታ ከአታካቹ ኑሯችን ከተባረረ መሀል ላይ ስንዋልል ጥሩ አይመስለኝም። ‹‹አይ አንተ ሁሌም አንድ ሐሳብ አያጣህም?›› አለችኝ ውዷ ባለቤቴ ማንጠግቦሽ፣ ‹‹ሳቅ አላማረሽም?›› ብዬ ብጠይቃት። በነገራችን ላይ ማንጠግቦሽ ከት ብላ ከሳቀች ድንበር ተሻጋሪ ድምጿን ማንም ነው ሚሰማው። አሁን ታዲያ በገባሁ በወጣሁ ቁጥር ‹‹ምነው ሰላም አይደላችሁም?›› የሚለኝ ሠፈርተኛ በዝቷል።  ይኼኔማ አንዳንዱ ተጣሉም ብሎ ያስወራ ይሆናል። ሰው እንዴት የሰውን ጓዳ ጎድጓዳ እየተከታተለ እንደሚኖር ሳስብ በእጅጉ ይደንቀኝ ጀመር። በነገራችን ላይ ከመሬት እየተነሳ ባለፀጋ የሚሆነው አልበዛባችሁም? መጠቃቀም በሕዝብ ሀብት ባይሆን ጥሩ ነው እያልን ብንመክር ብናስመክር ማን ከመጤፍ ቆጠረን? ‹‹ምርጫ ሲደርስ ብቻ የሚቆጠረው ድምፃችን ከወዲሁ ሰሚ ቢያገኝ ኖሮ የሌባው ቁጥር እንዲህ ባልበዛ ነበር፤›› ይለኛል የባሻዬ ልጅ በአንድ ጀንበር የሚከብሩ ሲበዙበት። መክበራቸው ሳያንስ ተፈርተው መኖራቸው የሚያበሳጨን አደባባይ ይቁጠረን። እናም ሳቅ ጠፋ የምለው በየትኛውም ሥፍራ እያረሩ መሳቅ የደስታ ምልክት ነው ተብሎ ስለማይቆጠር ነው።  ለነገሩ ዝም ብላችሁ ብትታዘቡ እንኳን መሳቅ ይቅርና እሪ ብሎ ማልቀስስ ተወዷል። (ቆይ የማይወደደው ምን ይሆን?) ‹‹ይኼ ለብ ማለት ደግ አይደለም አንበርብር፤›› ይሉኛል ባሻዬ ጋቢያቸውን እያጣፉ። ኑሯችን ከአንዱ ወደ አንዱ እንደኳስ እየጠለዘ ሲጫወትብን መሳቅ

አማራጭ ሐሳብና አማራጭ ጥንካሬ ያለው ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ ይፈለጋል!

Image
አገራችን ኢትዮጵያ ምን እንድትሆን ትፈልጋላችሁ ብንባል ቀጥተኛውና ቀልጣፋው መልሳችን የበለፀገችና ዲሞክራሲያዊት አገር እንድትሆን እንፈልጋለን ነው፡፡ ልማትና ዲሞክራሲ ጐን ለጐን ተያይዘውና ተሳስረው የሚታዩባት አገር እንድትሆን እንፈልጋለን፡፡ ልማት እንጂ ዲሞክራሲ አንፈልግም የሚለውን አንቀበልም፡፡ ዲሞክራሲ እንጂ ልማት አንፈልግም የሚለውንም አንቀበልም፡፡ ልማታዊና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት፣ መንግሥትና ፖለቲካ እንፈልጋለን፡፡ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እንፈልጋለን ስንል አንዱ መገለጫው የተለያዩ ሐሳቦች የሚንሸራሸሩበት ሥርዓት እውን ማድረግ ነው፡፡ ለአገር የሚጠቅም የተሻለ ሐሳብ አለን የሚሉ ኃይሎች የሚሰባሰቡበትና የሚደራጁበት የፖለቲካ ፓርቲ መፍጠርና ሥልጣን ለመያዝ መወዳደር መብት መሆኑን የሚያረጋግጥ ሥርዓት እውን ማድረግ ማለት ነው፡፡ ስለሆነም የፖለቲካ ፓርቲዎች መኖር ለአንድ አገር ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን መሆን ወሳኝ ነው፡፡ ሐሳቦች እርስ በርስ ይወዳደራሉ፤ ይታገላሉ፡፡ ሕዝቡም የተሻለውን ሐሳብ ይመርጣል፡፡ በሕዝብ ድምፅ የተመረጠውም አገሪቱን እንዲመራ ኃላፊነት ይሰጠዋል ማለት ነው፡፡ በዚህ ዙሪያ ሕዝብም፣ መንግሥትም፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችም በሥነ ሐሳብ ደረጃ ልዩነት የላቸውም፡፡ ሕዝብ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ኖረው ይወዳደሩ ብሎ ያምናል፡፡ በሕገ መንግሥቱም ሰፍሯል፡፡ በተግባር ግን የጠንካራ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ትግል፣ ፉክክርና ውድድር ማየት አልቻልንም፡፡ ጠንካራ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ እውን ማድረግ አልተቻለም፡፡ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አስፈላጊ የሆነው ጠንካራ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ በተግባር በኢትዮጵያ እውን መሆን አልቻለም፡፡ ለምን? ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጠንካራ መሆን ያልቻልነው ገዥው ፓርቲ እንዳንጠናከር ስላደረገን ነው የሚል መከራከሪያ ሊ

አሞራ ገደልና የዓሳ ገበያው

Image
በሔኖክ ረታ ቀደም ሲል አካባቢውን ለሚያውቀው ጎብኚ የአሞራ ገደል አሰያየም በቀጥታ ከአካባቢው ተፈጥሯዊ ሁኔታ ጋር ስለመዛመዱ መናገር ይችላል፡፡ ከከተማዋ ፈጣን ዕድገትና በየአቅጣጫው ከተስፋፋው የሥራ ዕድል ጋር ተያይዞ ግን ለከተማዋ ጀባ የተባለው ትኩረት ለዚህም የሐይቁ ታዋቂ ስፍራ እንደ ፀበል ደርሶ በመጠኑም ቢሆን የአጥር መከለያ ተሠርቶለትና ከዚህ በፊት እዚህም እዚያም ይጠባበስ የነበረው የዓሳ ምግብ በወጉ እየተዘጋጀ ለተመጋቢው መቅረብ ጀምሯል፡፡ እንደዚያም ሆኖ ግን ይህ ዝነኛ የሐይቁ ክፍል አሁንም ቢሆንም እንደሌላኛው የሐይቁ መዳረሻ በሰንደቅ ዓላማና በቀለማት ባሸበረቁ ጀልባዎች፣ አበቦችና የማስታወቂያ ሰሌዳዎች የደመቀ አይደለም፡፡ ይልቁንም ዓሳ ጎርጓሪ ወፎች፣ እነ አባ ኮዳ፣ አባጆፌዎችና ሌሎቹም ዓሳ ተመጋቢ ወፎች እንደትናንቱ ግቢውን ወረው፤ ከዓሳ አጥማጆች የሚያፈተልኩትን ጥቃቅን ዓሶችንና ከበላተኛው ተርፈው የተጣሉ ትርፍራፊዎችን እየተሻሙ ሲለቅሙ የሚታዩበት እንጂ፡፡ ለሁለት በተከፈለው ሰፊ ግቢ በአንደኛው በር የመግቢያ ትኬት እየተቆረጠበት በፓርክ (መናፈሻ) ውስጥ ፎቶግራፍ ለመነሣት የሚቻል ሲሆን በሌላኛው በር ደግሞ የዓሳ ጥብስና ሾርባን ለመመገብ ብቻ ታስቦ በነፃ የሚስተናገዱበት በር ይገኛል፡፡ በዚህ በር በስተግራ በኩል መደዳውን እንደ ሱቅ የተደረደሩት ደሳሳ ቤቶች እንደዋዛ በደረደሯቸው የመመገቢያ ጠረጴዛና ወንበሮች ተኮልኩሎ ለሚጠብቃቸው ተመጋቢ ፊሌቶ የተሰኘውን የአካባቢውን ተወዳጅ ዓሳ የሚጠበስባቸውና ሾርባው የሚዘጋጅባቸው ኩሽናዎች ናቸው፡፡ ‹‹ኧረ እባካችሁ! ቆየ እኮ!....›› ‹‹ሾርባው ይቅደም!›› ወዘተ የሚሉ የደንበኞች አቤቱታ በጭብጨባ ታጅበው ከዚህም ከዚያም ይሰማሉ፡፡ ጫጫታውና ግርግሩ በአንድ የሐ

Iodine Status and Cognitive Function of Mother-child Pairs in Sidama ...

Image
Iodine Status and Cognitive Function of Mother-child Pairs in Sidama ... By Alemtsehay Bogale Wotang

በሀይማኖት ተቋማት እና በግለሰብ እጅ ያሉ ጥንታዊ ፅሁፉችን የማሰባሰብና የማጥናት ስራ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

Image
የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት የኢትዮጵያን 12 ጥንታዊያን መጽሀፍትና የነገስታት ደብዳቤዎችን በዓለም የስነ ፁሑፍ ቅርስነት መዝግቦታል፡፡ አሁንም ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በአለም እውቅና ያላገኙትን የስነ ጽሁፍ ቅርሶች ለማስመዝገብና መስፈርቶቹን ለማወቅ የሚያስችላቸው ስልጠና በአዲስ አበባ እየተሰጠ ነው፡፡ ቅርሶቹ በአለም ቅርስነት ለመመዝገብ ዋነኛው መስፈርት አለም አቀፍ ይዘት ያላቸው ሊሆኑ ይገባል፡፡ በዩኔስኮ የአለም የስነ ጽሁፍ ቅርስ ፕሮግራም ማናጀር ጆይ ስፐሪንግ የአፍሪካ መገለጫ የሆኑ ቅርሶች ተጠብቀው ሊቆዩ ይገባል ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ ውያን   የራሳቸው የሆኑ ፊደል፣ ቁጥር እና የአጻጻፍ ስሌት ካላቸው ጥቂት የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ ናት፡፡ የተለያዩ የስነ ጽሁፍ ቅርሶችም ባለቤት ነች፡፡ ቅርሶች የአፍሪካ ትውስታ፣ ታሪክ፣ ባህልና ማንነት መገለጫ ናቸው፡፡ አፍሪካን አፍሪካ የሚያደርጓት ባለፉት ትውልዶች የተቀመጡ ታሪካዊ ዳራዎችና ቅርሶችን ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ ስትችል ነው፡፡ ይህን ማድረግ የሚቻለው ደግሞ ቅርሶቹን በሚገባ ጠብቆ ማቆየት ሲቻል ነው፡፡ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጽሀፍት ዋና ዳይሬክተር አቶ አብርሃም ሞቶሽ በሀይማኖት ተቋማት እና በግለሰብ እጅ ያሉ ጥንታዊ ጽሁፉችን የማሰባሰብና የማጥናት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በጊዜ ብዛት ይዞታቸውን ለመልቀቅ የተቃረቡትን ደግሞ በዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ስርዓት እየተቀየሩ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ ለ3 ቀናት የሚቆየውን ስልጠና በዩኔስኮ የደቡብ ኮሪያ ብሄራዊ ኮሚሽን እና የኮሪያ ባህላዊ ቅርሶች አስተዳደር ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻህፍት ኤጀንሲ ጋር በትብብር አዘጋጅተውታል፡