Posts

አሞራ ገደልና የዓሳ ገበያው

Image
በሔኖክ ረታ ቀደም ሲል አካባቢውን ለሚያውቀው ጎብኚ የአሞራ ገደል አሰያየም በቀጥታ ከአካባቢው ተፈጥሯዊ ሁኔታ ጋር ስለመዛመዱ መናገር ይችላል፡፡ ከከተማዋ ፈጣን ዕድገትና በየአቅጣጫው ከተስፋፋው የሥራ ዕድል ጋር ተያይዞ ግን ለከተማዋ ጀባ የተባለው ትኩረት ለዚህም የሐይቁ ታዋቂ ስፍራ እንደ ፀበል ደርሶ በመጠኑም ቢሆን የአጥር መከለያ ተሠርቶለትና ከዚህ በፊት እዚህም እዚያም ይጠባበስ የነበረው የዓሳ ምግብ በወጉ እየተዘጋጀ ለተመጋቢው መቅረብ ጀምሯል፡፡ እንደዚያም ሆኖ ግን ይህ ዝነኛ የሐይቁ ክፍል አሁንም ቢሆንም እንደሌላኛው የሐይቁ መዳረሻ በሰንደቅ ዓላማና በቀለማት ባሸበረቁ ጀልባዎች፣ አበቦችና የማስታወቂያ ሰሌዳዎች የደመቀ አይደለም፡፡ ይልቁንም ዓሳ ጎርጓሪ ወፎች፣ እነ አባ ኮዳ፣ አባጆፌዎችና ሌሎቹም ዓሳ ተመጋቢ ወፎች እንደትናንቱ ግቢውን ወረው፤ ከዓሳ አጥማጆች የሚያፈተልኩትን ጥቃቅን ዓሶችንና ከበላተኛው ተርፈው የተጣሉ ትርፍራፊዎችን እየተሻሙ ሲለቅሙ የሚታዩበት እንጂ፡፡ ለሁለት በተከፈለው ሰፊ ግቢ በአንደኛው በር የመግቢያ ትኬት እየተቆረጠበት በፓርክ (መናፈሻ) ውስጥ ፎቶግራፍ ለመነሣት የሚቻል ሲሆን በሌላኛው በር ደግሞ የዓሳ ጥብስና ሾርባን ለመመገብ ብቻ ታስቦ በነፃ የሚስተናገዱበት በር ይገኛል፡፡ በዚህ በር በስተግራ በኩል መደዳውን እንደ ሱቅ የተደረደሩት ደሳሳ ቤቶች እንደዋዛ በደረደሯቸው የመመገቢያ ጠረጴዛና ወንበሮች ተኮልኩሎ ለሚጠብቃቸው ተመጋቢ ፊሌቶ የተሰኘውን የአካባቢውን ተወዳጅ ዓሳ የሚጠበስባቸውና ሾርባው የሚዘጋጅባቸው ኩሽናዎች ናቸው፡፡ ‹‹ኧረ እባካችሁ! ቆየ እኮ!....›› ‹‹ሾርባው ይቅደም!›› ወዘተ የሚሉ የደንበኞች አቤቱታ በጭብጨባ ታጅበው ከዚህም ከዚያም ይሰማሉ፡፡ ጫጫታውና ግርግሩ በአንድ የሐ

Iodine Status and Cognitive Function of Mother-child Pairs in Sidama ...

Image
Iodine Status and Cognitive Function of Mother-child Pairs in Sidama ... By Alemtsehay Bogale Wotang

በሀይማኖት ተቋማት እና በግለሰብ እጅ ያሉ ጥንታዊ ፅሁፉችን የማሰባሰብና የማጥናት ስራ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

Image
የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት የኢትዮጵያን 12 ጥንታዊያን መጽሀፍትና የነገስታት ደብዳቤዎችን በዓለም የስነ ፁሑፍ ቅርስነት መዝግቦታል፡፡ አሁንም ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት በአለም እውቅና ያላገኙትን የስነ ጽሁፍ ቅርሶች ለማስመዝገብና መስፈርቶቹን ለማወቅ የሚያስችላቸው ስልጠና በአዲስ አበባ እየተሰጠ ነው፡፡ ቅርሶቹ በአለም ቅርስነት ለመመዝገብ ዋነኛው መስፈርት አለም አቀፍ ይዘት ያላቸው ሊሆኑ ይገባል፡፡ በዩኔስኮ የአለም የስነ ጽሁፍ ቅርስ ፕሮግራም ማናጀር ጆይ ስፐሪንግ የአፍሪካ መገለጫ የሆኑ ቅርሶች ተጠብቀው ሊቆዩ ይገባል ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ ውያን   የራሳቸው የሆኑ ፊደል፣ ቁጥር እና የአጻጻፍ ስሌት ካላቸው ጥቂት የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ ናት፡፡ የተለያዩ የስነ ጽሁፍ ቅርሶችም ባለቤት ነች፡፡ ቅርሶች የአፍሪካ ትውስታ፣ ታሪክ፣ ባህልና ማንነት መገለጫ ናቸው፡፡ አፍሪካን አፍሪካ የሚያደርጓት ባለፉት ትውልዶች የተቀመጡ ታሪካዊ ዳራዎችና ቅርሶችን ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ ስትችል ነው፡፡ ይህን ማድረግ የሚቻለው ደግሞ ቅርሶቹን በሚገባ ጠብቆ ማቆየት ሲቻል ነው፡፡ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጽሀፍት ዋና ዳይሬክተር አቶ አብርሃም ሞቶሽ በሀይማኖት ተቋማት እና በግለሰብ እጅ ያሉ ጥንታዊ ጽሁፉችን የማሰባሰብና የማጥናት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በጊዜ ብዛት ይዞታቸውን ለመልቀቅ የተቃረቡትን ደግሞ በዘመናዊ የመረጃ አያያዝ ስርዓት እየተቀየሩ መሆኑን ይገልጻሉ፡፡ ለ3 ቀናት የሚቆየውን ስልጠና በዩኔስኮ የደቡብ ኮሪያ ብሄራዊ ኮሚሽን እና የኮሪያ ባህላዊ ቅርሶች አስተዳደር ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻህፍት ኤጀንሲ ጋር በትብብር አዘጋጅተውታል፡

It does not relate to us.

Image
Asfaw Dingamo, deputy director and advisor to the director general of the Ethiopian Sugar Corporation, Abaye Tsehaye, said this speaking about the delay in construction of Tendaho Sugar Factory, whose first phase was reportedly meant to be completed in 2010 and its second phase a year after. If the question is whether the contractor had an implementation problem, I would say yes, Asfaw told Sendeke, an Amharic weekly, in an exclusive interview published on Wednesday, November 28, 2012. http://addisfortune.net/columns/it-does-not-relate-to-us/

ለሥርዓትና ለተቋማት ግንባታ ቅድሚያ ትኩረትና ርብርብ ይደረግ!!

Image
ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን መሆን፣ ለልማት፣ ለሰላምና መረጋጋት፣ ለአገር ህልውናና ደኅንነት እጅግ በጣም ወሳኝ መሆኑ በተደጋጋሚ መነገሩ ቢሰለችም፣ አሁንም እንደገና ቅድሚያ ርብርብና ልዩ ትኩረት ለሥርዓትና ለተቋማት ግንባታ ይሰጥ እንላለን፡፡ አገራችን ኢትዮጵያ እንዴት መኖርና መንቀሳቀስ እንዳለባት የሚመራ ሕገ መንግሥት አላት፡፡ ሕገ መንግሥቱን ሥራ ላይ ለማዋል የወጡ በርካታ ሕጎች አሉ፡፡ አዋጆቹንና ሕጎቹን ሥራ ላይ ለማዋል ይበጃል የተባሉ ደንቦችና መመርያዎችም በብዛት አሉ፡፡ ከየት ጀምረን የት እንድረስ በማለት የተለያዩ ዕቅዶች ወጥተዋል፡፡ የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድም አለ፡፡ ህዳሴውን እውን ያደርጋሉ ተብለው የተቀመጡ ራዕዮችም አሉ፡፡ እነዚህን ሥራ ላይ የሚያውላቸው ግን ማን ነው? ሥራ ላይ የሚውሉትስ እንዴት ነው? ሥራ ላይ በትክክል መዋላቸውና አለመዋላቸው የሚታወቀውስ እንዴት ነው? ዋስትናቸው ምንድን ነው? ለእነዚህ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ስንሞክር ነው በኢትዮጵያ ተቋማት ያልተገነቡ መሆናቸውን፣ ሥርዓት ተፈጥሮላቸውና ሥርዓቱን ተከትለው የማይሠሩ መሆናቸው በግልጽ የሚታየው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የመንግሥትና የግል ባንኮችን የሚከታተልና የሚቆጣጠር አካል ነው የሚል ሕግ አለ፡፡ እንደ ተቋም ይህን ኃላፊነት እንዲወጣ ሕግ ያስገድደዋል፡፡ በተግባር ግን ይህን ይፈጽማል? ደፈር ብሎ እንትን የተባለ ባንክን ይቆጣጠራል፤ ያዛል፡፡ ፈርቶ ደግሞ እንትን የተባለ ባንክን ለመቆጣጠር ይሽመደመዳል፡፡ አንዱ ባንክ ዞር በል ሲለው ያዙኝ ልቀቁኝ ይላል፡፡ ሌላው ባንክ ዞር በል ሲለው እውነትም በፍርኃት ዞር ይላል፡፡ እንደ ተቋም አይንቀሳቀስም፡፡ ወጥ ሥርዓት አይከተልም፡፡ መሬት የሚሰጠውና የሚቀማው ማዘጋጃ ቤት ነው፡፡ ሕግን ተከትሎ፡፡