ሐዋሳ ከነማ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የደረጃ ሰንጠረዥ መሪ ሆነ
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መለስ ዋንጫ ረቡዕ ህዳር 26/2005 በተከናወነው ጨዋታዎች ሐዋሳ ከነማ እና ደደቢት ድል ሲቀናቸው መብራት ኃይልና ኢትዮጵያ ቡና ነጥብ ጥለዋል። በዘጠነኛው ሳንምት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በዕለቱ አምስት ጨዋታዎች ተከናውነዋል።ከነዚህ መካከል ሐዋሳ ላይ ሐዋሳ ከነማ አርባምንጭ ከነማን ያስተናገደበት ጨዋታ ከፍተኛ ግምት አግኝቶ ነበር። የፕሪምየር ሊጉ መሪ የነበረው ቅዱስ ጊዩርጊስ ህዳር 25/2005 ሐረር ላይ ከሐረር ቢራ ጋር ተጫውቶ ነጥብ ጥሎ በመመለሱ ምክንያት ሐዋሳ መሪነቱን የሚረከብበት መልካም አጋጣሚ ይዞ ነበር ወደ ሜዳ የገባው። ዘንድሮ ጥሩ እንቅስቃሴ እያሳየ ያለው ሐዋሳ የደቡብ ደርቢውን ጨዋታ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በመርታት ለወራት ያክል የደረጃ አናት ላይ የሚሆንበት ጣፋጭ ድል ይዞ ወጥቷል።ብሩክ አየለ የሐዋሳ ከነማን ሁለቱንም ግቦች ሲያስቆጥር በረከት ዳሙ ደግሞ የአርባምንጭን ብቸኛ ግብ ከመረብ አገናኝቷል። ከህዳር 27/2005 ጀምሮ ለብሔራዊ ቡድኑ ዝግጅትና አፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ ሲባል የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች ስለሚቆረጡ ሐዋሳ ከነማ መሪነቱን ይዞ ለበረካታ ሳምንታት ይቆያል። ወደ አዳማ ከነማ ተጉዞ በአዳማው አበበ ቢቂላ ሰታዲየም ውጤት የራቀውን አዳማ ከነማን የገጠመው ደደቢትም 3ለ1 አሸንፎ ተመልሷል።ጌታነህ ከበደ ለደደቢት ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል። በዚህም የሊጉን ከኮከብ ግብ አግቢነት በብቸኝነት ይመራል።በኃይሉ አሰፋ ቀሪዋን የደደቢት ግብ አስቆጥሯል። በውጤቱም ደደቢት ከቅዱስ ጊዩርጊስ እኩል 18 ነጥብ በመያዝ በግብ ክፍያ በልጦ ሁለተኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችላል። ወደ አሰላ ተጉዞ የነበረው ኢትዮጵያ ቡና ከሙገር ሲምንቶ ጋር ያለምንም ግብ በመለያየት ሁለት