የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በክልል ደረጃ ሲዳማ ዞን በይርጋዓለም ከተማ በድምቀት ተከበረ
ሃዋሳ ህዳር 25/2005 ህገ መንግስቱ የፈጠራቸው መልካም ሁኔታዎችን በመጠቀም የተጀመረውን የጸረ ድህነት ዘመቻ በማጠናከር የመለስን ራዕይ እውን ለማድረግ የክልሉ ህዝብ በጋራ ጠንክሮ መስራት እንዳለበት የደቡብ ክልል ምክር አፈ ጉባዔ አስገነዘቡ፡፡ ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ የሚከበረውን የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ቀን በክልል ደረጃ ሲዳማ ዞን በይርጋዓለም ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ትናንት በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል፡፡ አፈጉባዔ ወይዘሮ ገነት ወልዴ ፕሮግራሙን ሲከፍቱ እንደተናገሩት ህገ መንግስቱ የፈጠራቸውን ምቹና መልካም ሁኔታዎችን በመጠቀም ድህነትን ለማስወገድና የመልካም አስተዳደር ለማስፈን በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የተቀየሱ የልማት ራዕዮችን እውን ለማድረግ ሁሉም በጋራ ጠንክሮ ሊሰራ ይገባል፡፡ ህዳር 29 ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች በልዩነታቸው ውበትን፣ በውበታቸው አንድነትን የመሰረቱበት ብቻ ሳይሆን ባህል፣ ወግ፣ ልማዳቸውንና ቱውፊታቸውን ያደሱበት ልዩና ታሪካዊ ቀን ነው ብለዋል፡፡ የክልሉ ህዝብ በህገ መንግስቱ የተጎናጸፈውን ራስን በራስ የማሰተዳደር ነፃነት በመጠቀም ባለፉት 21 ዓመታት በርካታ የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የሰላም ድሎችን ሊያስመገብ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ መሃንዲስነት የተዘረጉትን የልማት መስመሮችንና መልካም ፖሊሲዎችን በማስቀጠል ድህነትን ታሪክ አድርጎ ለማለፍ ዘርፈ ብዙ ጥረቶች መደረጋቸውን ጠቁመው በመስኩ አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል፡፡ ወይዘሮ ገነት በማያያዝም በክልሉ ብሎም በሀገሪቱ ዘላቂና ቀጣይነት ያለውን ልማት በማስመዝገብ ድህነትን ለማስወገድ ለተያዘው ዕቅድ መሳካት አመራሩ፣ መምህራን፣ ተማሪዎች፣ ወጣቶችና ሌሎች የህብተሰብ ክፍሎች በየተ