Posts

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲሱ የካቢኔ አደረጃጀት እያነጋገረ ነው

Image
-    ካቢኔው በሕገ መንግሥቱ መሠረት አንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ይኖረዋል -    የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ ያላቸው ሁለት ባለሥልጣናት ተሹመዋል -    አዲሱ አደረጃጀት ከሌሎች ሕጐች ጋር ተቃርኖ አለው እየተባለ ነው በዮሐንስ አንበርብር የሥራ አስፈጻሚውን ከፍተኛ ሥልጣን በማግኘት አገሪቱን መምራት ከጀመሩ ሁለት ወራት ከቀናት ያስቆጠሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሰሞኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመቅረብ ካቢኔያቸውን በአዲስ መልክ እንዳደራጁ አስታውቀዋል፡፡ በዚህም መሠረት የሁለት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችንና የሌሎች ሚኒስትሮችን ሹመት አፀድቀዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲሱ የካቢኔ አደረጃጀትም መነጋገሪያ ሆኗል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት የሚኒስትሮች ምክር ቤት (ካቢኔ) በሕገ መንግሥቱና በመመሥረቻ አዋጁ የተጣለበትን ኃላፊነቶች በብቃት ለመወጣትና የአስፈጻሚነት ሚናውን በአግባቡ እንዲወጣ ለማድረግ፣ እንደ አዲስ በሦስት ዘርፎች መዋቀሩ አስፈላጊ መሆኑን ለፓርላማው አስታውቀዋል፡፡ በዚህም መሠረት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዲፕሎማሲ፣ የደኅንነት፣ የመከላከያ እንዲሁም ከፍተኛና ግዙፍ (ሜጋ) ፕሮጀክቶችን በቀጥታ እንዲከታተሉ ተደርጓል፡፡ ከዚህ ውጪ ያሉ አስፈጻሚው የሚከታተላቸውን ተግባራት በብቃት ለመምራት የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሦስት ዘርፎች እንዲዋቀር መደረጉን ገልጸዋል፡፡ ማኅበራዊ ጉዳዮችን፣ መልካም አስተዳደርና ረፎርምን፣ ፋይናንስና ኢኮኖሚን የሚመለከቱ ሦስት የሥራ ዘርፎች በአዲሱ የካቢኔ መዋቅር የተፈጠሩ ሲሆን፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የትምህርት ሚኒስትሩ ደመቀ መኮንን የማኅበራዊ ዘርፉን የሚመሩ መሆኑ ታውቋል፡፡ ከዚህ ቀደም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ቢሮን በሚኒስት

ሲዳማ በዚህ ሳምንት የሬዲዮ ፕሮግራም በሲኣን 4 መደበኛ ጉባኤ ላይ ሰፊ ዘጋባ ይዞል

Image
The Nomonanoto Show

ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሹመቱ ህገመንግስቱን የሚጋፋ ነው አሉ

Written by  መታሰቢያ ካሳዬ ኃላፊነቴን ከህዝቡ ጋር በአግባቡ እወጣለሁ - ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ሹመቱ ኢህአዴግ ያለበትን የፖለቲካ ሽኩቻ ለማስታገስ ያደረገው ነው የተሰጠው ሹመት በብቃት ላይ የተመሰረተ አይደለም ሹመቱ የቀድሞ ጠቅላይ ሚ/ር አሻራ አለበት (ተቃዋሚዎች) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከትናንት በስቲያ ያፀደቀውን የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት፣ የንግድ ሚኒስትርነት፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትርነትና ሌሎች ሹመቶችን አስመልክቶ ሹመቱ በአግባቡና በሥርዓት ያልተሰጠና ህጋዊ ሥርዓት የሚጐድለው ነው ሲሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተናገሩ፡፡ ሹመቱ ህገመንግስቱን የሚጋፋና ከህግና ሥርዓት ውጪ የተሰጠ ነው ሲሉም ተችተውታል፡፡ በአንድ ድምፀ ተአቅቦና በሙሉ ድምጽ ድጋፍ በፀደቀው ሹመት መሠረት ሁለት ተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትሮችም ተሹመዋል፡፡ ከትናንት በስቲያ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተከናወነው ሥነሥርዓት ሹመታቸው የፀደቀላቸው አቶ ሙክታር ከድር በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር እና ሪፎርም ክላስተር አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በምክትል ጠቅላይ ሚ/ር ማዕረግ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ አቶ ታደለ ጫኔ የንግድ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና ዶ/ር ከስተብርሃን አድማሱ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል፡፡ ብቸኛው የመድረክ ተወካይና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ በሹመቱ ወቅት ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል፡፡ አቶ ግርማ ድምፀ ተአቅቦ ያደረጉበትን ምክንያት ሲናገሩም፤ ሹመቱ ከመሰጠቱ በፊት ስለተሿሚዎቹ ለም

አወቃቀሩ የህወሐትን የሥልጣን የበላይነት የሚያስጠብቅ ነው

Image
ጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ ለምክር ቤቱ አቅርበው ያፀደቁትን አዲስ የካቢኔ አደረጃጀት እንዴት ያዩታል? ከዚህ በፊት ሰምቼ ነበር፤ ሶስት ቦታ እንክፈለው የሚለውን፡፡ በዛን ጊዜ ግን ስምምነት ላይ አልተደረሰም፡፡ በአንድ ነገር ላይ ግን ስምምነት ላይ ተደርሶ ነበር፡፡ አዲስ የሚመጣው ጠ/ሚኒስትር ማንም ይሁን ማን ከዚህ በፊት የነበረው ጠ/ሚ የነበረውን ሃይል ክምችት ይዞ መቀጠል እንደማይችል ተነጋግረው ጨርሰዋል፡፡ ማን ጠ/ሚ ይሆናል የሚለው አይደለም ወሳኙ፤ ህወሓት አካባቢ ማን እየተሾመ ነው የሚል ነው ወሳኙ፡፡ አሁንም ቢሆን ምንም ወዲያና ወዲህ የለኝም፡፡ በእኔ ግምት ሕወሓት አሁንም ቢሆን ስትራቴጂካዊ ቦታ ላይ ተቀምጧል - ጠ/ሚ ለመሆን፡፡ በሁለት መንገድ ነው እየሄዱ ያሉት፡፡ በውጭ ጉዳይም ትክክለኛ የስልጣን ቅብብል ነው የሚባለው ጉዳይ አሁን ጥያቄ ውስጥ የገባ መሰለኝ፡፡ ህወሓት ከያዘው ቁልፍ የሚኒስቴር መ/ቤቶች ስልጣን አኳያ ከሁለት ዓመት ተኩል በኋላ ሊሆን የሚችለውን ለመገመት ስንሞክር አመራሩ እንደ ዱላ ቅብብል ነው የሚባለው ጥያቄ ውስጥ የገባ ይመስለኛል፡፡ ወሳኝ ወሳኝ ቦታዎችን ወስደዋል፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሄዷል፤ እዛው ተመልሶ ቦታው ገብቷል፡፡ ወሳኝ የሚባለው የፋይናንስና ኢኮኖሚው ሄዷል፤ ተመልሶ ቦታው ገብቷል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት የጠ/ሚኒስትርነት ስልጣኑ (ቢሮ) የተጠናከረ ነውና ለሶስት መክፈል አለብን የሚል ሃሳብ ተነስቶ ነበር፡፡ በጊዜው ያ ተቀባይነት አላገኘም፡፡ የጠ/ሚ ቦታ ከህወሓት እጅ ከወጣ የህወሓት የበላይነት ያከትማል የሚል ስጋት ነበራቸው፡፡ አሁን እንግዲህ አንድ ጠ/ሚኒስትርና ሦስት ምክትል ጠ/ሚኒስትሮች አሉን ማለት ነው፡፡ እያንዳንዳቸው ደግሞ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በክላስተር ተከፋፍለው አስተባባሪነት ተሾሞባቸዋል

የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ቀን በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከትናንት ጀምሮ በድምቀት አየተከበረ ነው

Image
ሃዋሳ ህዳር 22/2005 ህገ መንግሰቱ የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የተጀመረውን የፀረ ድህነት ዘመቻና የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ራዕይ ከዳር ለማድረስ ህብረተሰቡ በጋራ ጠንክሮ መስራት እንዳለበት የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት አስገነዘቡ ። ለሰባተኛ ጊዜ የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዩኒቨርሲቲው ግቢ ከትናንት ጀምሮ በተለያየ ዝግጅት በድምቀት እየተከበረ ነው ። ፕሬዚዳንቱ ዶክተር ዮሰፍ ማሞ በአሉን አስመልክቶ የተዘጋጀውን የፓናል ውይይት ሲከፍቱ እንደተናገሩት ህገ መንግስቱ የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ድህነትን ለማስወገድና በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የተቀየሱ የልማት ራዕዮችን ለማሳካት ሁሉም በጋራ ጠንክሮ ሊሰራ ይገባል። የክልሉ ህዝብና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በህገ መንግሰቱ የተጎናፀፈውን ራስን በራስ የማስተዳደር ነፃነት በመጠቀም ባለፉት ሃያ አንድ አመታት በርካታ የልማት ድሎችን ሊያስመዘግብ መቻሉን አስታዉቀዋል ። በሀገሪቱ ዘላቂና ቀጣይነት ያለው ልማት በማስመዝገብ ድህነት ለማስወገድ ለተያዘው እቅድ መሳካት ሁሉም በየተሰማራበት ጠንክሮ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። በአሉ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ለዘመናት ሲያነሱት የነበረው የነፃነትና የእኩልነት መብት ጥያቄ ምላሽ ያገኘበት ዕለት በመሆኑ በአሉ ለዘላለም ሲዘከር ይኖራል ብለዋል ። የፌደሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፌ ጉባኤ አቶ መሃመድ ረሽድ በበኩላቸዉ በሀገሪቱ ሁሉም አከባቢ እየተካሄዱ ያሉትን የልማት ጅምሮች በማፋጠን ዋንኛ ጠላት የሆነውን ድህነት ድል ለመንሳት የሁሉም አካላት የተቀናጀ ጥረት ይጠይቃል ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች በመፈቃቀር ላይ የመሰረቱትን አንድነታቸውን በማጠናከር ባለፉት አመታት በድህነት ላይ በጋራ በከፈቱት ዘመቻ በ