Posts

ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሹመቱ ህገመንግስቱን የሚጋፋ ነው አሉ

Written by  መታሰቢያ ካሳዬ ኃላፊነቴን ከህዝቡ ጋር በአግባቡ እወጣለሁ - ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ሹመቱ ኢህአዴግ ያለበትን የፖለቲካ ሽኩቻ ለማስታገስ ያደረገው ነው የተሰጠው ሹመት በብቃት ላይ የተመሰረተ አይደለም ሹመቱ የቀድሞ ጠቅላይ ሚ/ር አሻራ አለበት (ተቃዋሚዎች) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከትናንት በስቲያ ያፀደቀውን የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት፣ የንግድ ሚኒስትርነት፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትርነትና ሌሎች ሹመቶችን አስመልክቶ ሹመቱ በአግባቡና በሥርዓት ያልተሰጠና ህጋዊ ሥርዓት የሚጐድለው ነው ሲሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተናገሩ፡፡ ሹመቱ ህገመንግስቱን የሚጋፋና ከህግና ሥርዓት ውጪ የተሰጠ ነው ሲሉም ተችተውታል፡፡ በአንድ ድምፀ ተአቅቦና በሙሉ ድምጽ ድጋፍ በፀደቀው ሹመት መሠረት ሁለት ተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትሮችም ተሹመዋል፡፡ ከትናንት በስቲያ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተከናወነው ሥነሥርዓት ሹመታቸው የፀደቀላቸው አቶ ሙክታር ከድር በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር እና ሪፎርም ክላስተር አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በምክትል ጠቅላይ ሚ/ር ማዕረግ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር፣ አቶ ታደለ ጫኔ የንግድ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና ዶ/ር ከስተብርሃን አድማሱ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል፡፡ ብቸኛው የመድረክ ተወካይና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ በሹመቱ ወቅት ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል፡፡ አቶ ግርማ ድምፀ ተአቅቦ ያደረጉበትን ምክንያት ሲናገሩም፤ ሹመቱ ከመሰጠቱ በፊት ስለተሿሚዎቹ ለም

አወቃቀሩ የህወሐትን የሥልጣን የበላይነት የሚያስጠብቅ ነው

Image
ጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ ለምክር ቤቱ አቅርበው ያፀደቁትን አዲስ የካቢኔ አደረጃጀት እንዴት ያዩታል? ከዚህ በፊት ሰምቼ ነበር፤ ሶስት ቦታ እንክፈለው የሚለውን፡፡ በዛን ጊዜ ግን ስምምነት ላይ አልተደረሰም፡፡ በአንድ ነገር ላይ ግን ስምምነት ላይ ተደርሶ ነበር፡፡ አዲስ የሚመጣው ጠ/ሚኒስትር ማንም ይሁን ማን ከዚህ በፊት የነበረው ጠ/ሚ የነበረውን ሃይል ክምችት ይዞ መቀጠል እንደማይችል ተነጋግረው ጨርሰዋል፡፡ ማን ጠ/ሚ ይሆናል የሚለው አይደለም ወሳኙ፤ ህወሓት አካባቢ ማን እየተሾመ ነው የሚል ነው ወሳኙ፡፡ አሁንም ቢሆን ምንም ወዲያና ወዲህ የለኝም፡፡ በእኔ ግምት ሕወሓት አሁንም ቢሆን ስትራቴጂካዊ ቦታ ላይ ተቀምጧል - ጠ/ሚ ለመሆን፡፡ በሁለት መንገድ ነው እየሄዱ ያሉት፡፡ በውጭ ጉዳይም ትክክለኛ የስልጣን ቅብብል ነው የሚባለው ጉዳይ አሁን ጥያቄ ውስጥ የገባ መሰለኝ፡፡ ህወሓት ከያዘው ቁልፍ የሚኒስቴር መ/ቤቶች ስልጣን አኳያ ከሁለት ዓመት ተኩል በኋላ ሊሆን የሚችለውን ለመገመት ስንሞክር አመራሩ እንደ ዱላ ቅብብል ነው የሚባለው ጥያቄ ውስጥ የገባ ይመስለኛል፡፡ ወሳኝ ወሳኝ ቦታዎችን ወስደዋል፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሄዷል፤ እዛው ተመልሶ ቦታው ገብቷል፡፡ ወሳኝ የሚባለው የፋይናንስና ኢኮኖሚው ሄዷል፤ ተመልሶ ቦታው ገብቷል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት የጠ/ሚኒስትርነት ስልጣኑ (ቢሮ) የተጠናከረ ነውና ለሶስት መክፈል አለብን የሚል ሃሳብ ተነስቶ ነበር፡፡ በጊዜው ያ ተቀባይነት አላገኘም፡፡ የጠ/ሚ ቦታ ከህወሓት እጅ ከወጣ የህወሓት የበላይነት ያከትማል የሚል ስጋት ነበራቸው፡፡ አሁን እንግዲህ አንድ ጠ/ሚኒስትርና ሦስት ምክትል ጠ/ሚኒስትሮች አሉን ማለት ነው፡፡ እያንዳንዳቸው ደግሞ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በክላስተር ተከፋፍለው አስተባባሪነት ተሾሞባቸዋል

የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ቀን በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከትናንት ጀምሮ በድምቀት አየተከበረ ነው

Image
ሃዋሳ ህዳር 22/2005 ህገ መንግሰቱ የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የተጀመረውን የፀረ ድህነት ዘመቻና የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ራዕይ ከዳር ለማድረስ ህብረተሰቡ በጋራ ጠንክሮ መስራት እንዳለበት የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት አስገነዘቡ ። ለሰባተኛ ጊዜ የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዩኒቨርሲቲው ግቢ ከትናንት ጀምሮ በተለያየ ዝግጅት በድምቀት እየተከበረ ነው ። ፕሬዚዳንቱ ዶክተር ዮሰፍ ማሞ በአሉን አስመልክቶ የተዘጋጀውን የፓናል ውይይት ሲከፍቱ እንደተናገሩት ህገ መንግስቱ የፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም ድህነትን ለማስወገድና በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የተቀየሱ የልማት ራዕዮችን ለማሳካት ሁሉም በጋራ ጠንክሮ ሊሰራ ይገባል። የክልሉ ህዝብና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በህገ መንግሰቱ የተጎናፀፈውን ራስን በራስ የማስተዳደር ነፃነት በመጠቀም ባለፉት ሃያ አንድ አመታት በርካታ የልማት ድሎችን ሊያስመዘግብ መቻሉን አስታዉቀዋል ። በሀገሪቱ ዘላቂና ቀጣይነት ያለው ልማት በማስመዝገብ ድህነት ለማስወገድ ለተያዘው እቅድ መሳካት ሁሉም በየተሰማራበት ጠንክሮ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። በአሉ የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ለዘመናት ሲያነሱት የነበረው የነፃነትና የእኩልነት መብት ጥያቄ ምላሽ ያገኘበት ዕለት በመሆኑ በአሉ ለዘላለም ሲዘከር ይኖራል ብለዋል ። የፌደሬሽን ምክር ቤት ምክትል አፌ ጉባኤ አቶ መሃመድ ረሽድ በበኩላቸዉ በሀገሪቱ ሁሉም አከባቢ እየተካሄዱ ያሉትን የልማት ጅምሮች በማፋጠን ዋንኛ ጠላት የሆነውን ድህነት ድል ለመንሳት የሁሉም አካላት የተቀናጀ ጥረት ይጠይቃል ብለዋል። የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች በመፈቃቀር ላይ የመሰረቱትን አንድነታቸውን በማጠናከር ባለፉት አመታት በድህነት ላይ በጋራ በከፈቱት ዘመቻ በ

በሀዋሳ ከተማ ከ210 ሚልዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የልማት ስራዎች እየተካሄዱ ናቸዉ -በከተሞች ሳምንት ላይ ለተሳተፉ የምስክር ወረቀት ተሰጠ

Image
አዋሳ ህዳር 21/2005 በሀዋሳ ከተማ ከ210 ሚልዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተለያዩ የመሰረተ ልማት ስራዎች ግንባታ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ የከተማው አስተዳደር ገለጸ፡፡ በአራተኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ሳምንት ሀዋሳ ከተማ ላስመዘገበችው አመርቂ ውጤት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማት፣ ድርጅቶች፣ ማህበራትና ግለሰቦች ትናንት ምሽት የምስጋና ምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡ የከተማው ከንቲባ አቶ ዮናስ ዮሴፍ በዚሁ የምስጋና ፕሮግራም ላይ እንደተናገሩት ከተማዋን ለነዋሪው ምቹ፣ የኢንቨስትመንት ተመራጭ እንዲሁም የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ በርካታ የልማት ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸዉ ። ሀዋሳ ውብ፣ ጽዱና አረንጓዴ፣ በሀገርና በአለም አቀፍ ደረጃ ገጽታዋ የጎላ እንዲሆን የቱሪስት ፍሰቱ እንዲጨምር፣ የንግድና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል ። በከተማ አስተዳደር፣ በማዘጋጃ ቤት የውስጥ ገቢ፣ በመንግስት መደበኛ በጀትና ከአጋር ድርጅቶች በተመደበው 210 ሚልዮን ብር ወጪ እየተካሄዱ ያሉት 10 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ ፣ ከ45 ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ የጠጠርና የኮብል ስቶን ንጣፍ ናቸዉ ። በተጨማሪ የባህል ማዕከል፣ ዘመናዊ የመንገድ ላይ መብራትና የውሃ መስመር ዝርጋታዎች፣ እንዲሁም ዘመናዊ ቄራ ግንባታ በዋናነት እንደሚገኙበት አቶ ዮናስ ተናግረዋል፡፡ ከመሰረተ ልማት ግንባታዎች ውስጥ እስከ አሁን አብዛኛዎቹ ከ50 በመቶ በላይ መከናወናቸዉንና በጀት ዓመቱ ከፍፃሜ ለማድረስ ጥረት ከወዲሁ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል፡፡ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ታገሰ ጫፎ ለተቋማቱ፣ ድርጅቶችና ማህበራት ሰርተፍኬት ከሰጡ በኋላ ባስተላለፉት መልዕክት በአመራሩና ከተማ ነዋሪዎች የጋራ ጥረት የተመዘገበ ውጤት በ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአምስት ሚኒስትሮች ሹመትን አጸደቀ

Image
አዲስ አበባ ህዳር 20/2005 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አምስት የፌዴራል አስፈጻሚ አካላት የሥራ ኃላፊዎች ሹመትን አጸደቀ። ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው የ3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ስብሰባ የሁለት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የንግድ ሚኒስትርና የጤና ጥበቃ ሚኒስትሮችን ሹመት አጽድቋል። በዘህም መሰረት አቶ ሙክታር ከድር በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ማሻሻያ ዘርፍ አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር፣ ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የፋይናንስና የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪና የመገናኛና ኢንፎርሜሽን መገናኛና ሚኒስትር በመሆን ተሹመዋል። ይህም ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ሦስት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች እንዲኖሯት ያስቻለ ሹመት ሆኗል፡፡ እንዲሁም የጤና ጥበቃ ሚኒስትር የነበሩት ዶክተር ቴድሮስ አድሓኖም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ የንግድ ተጠባባቂ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ከበደ ጫኔ የንግድ ሚኒስትር ሆነው ሲሾሙ ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል። ተሿሚዎቹ በትምህርት ዝግጅታቸው፣ በፖለቲካ አመራር ብቃታቸውና ባላቸው የስራ ልምድ ለኃላፊነቱ የተመረጡ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት አሁን የተካሄደው ሹመት የሚኒስትሮች ምክር ቤትን ለማጠናከር፣ የተሻለ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብና የመተካካት ሥርዓቱን ለማጎልበት ነው። ሹመቱ በአንድ ድምፀ ተአቅቦና በአብላጫ ድምጽ የጸደቀ ሲሆን ተሿሚዎቹም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት በአቶ ተገኔ ጌታነህ አማካይነት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል፡፡ በተጨማሪ ምክር በኢትዮጵያ መንግሥትና በዓለም አቀፍ የልማት ማህበር መካካል 4ኛውን የመንገድ ዘር