ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ምርትና ምርታማነት በመጨመር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችል የግብርና ቴክኖሎጂ እያስተዋወቀ ነው
አዋሳ ህዳር 18/2005 የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነትን ለመጨመርና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከ11 የሚበልጡ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ በማስተዋወቅ ላይ እንደሚገኝ የሀዋሳ ዩነቪርስቲ ገለጸ፡፡ በዩኒቨርስቲው በሲዳማና ገዴኦ ዞኖች በሙከራ ደረጃ እየተሰሩ ያሉ ቴክኖሎጅዎችን የማላመድ፣ የማስተዋወቅና የማስፋፋት ስራዎች ሰሞኑን ተጎብኝቷል፡፡ የዩኒቨርስቲ አካዳሚና ምርምር ምክትል ፕሬዜዳንት ዶክተር ፍቅሬ ደሳለኝ በጉብኝት ወቅት እንደገለጹት በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ መጨረሻ የግብርና ምርት በእጥፍ ለማሳደግ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ዝርያዎችን ለማላመድና ማስፋፋት ስራ ዩኒቨርስቲው ትኩረት ተሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡ ዩኒቨርስቲው በሀገሪቱ የግብርና ምርታማነትን ለማሻሻል የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ የሚያግዙና በምርምር ጣቢያ ምርታማነታቸው የተረጋገጠ 11 ዝርያዎችን በክልሉ አራት ወረዳዎች የማባዛትና የማላመድ ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በልጆች ላይ የሚከሰተውን የቫይታሚን ኤ ንጥረ ምግብ እጥረት የሚከላከሉ ሰብሎች፣ የቤተሰብ ገቢና የምግብ ዋስትናን ለማሻሻል የሚያግዙ፣ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ፣ የአንስሳት መኖ፣ ሀገር በቀል የበግና ፍየል ዝርያዎችን የማዳቀልና ማባዛት እንዲሁም መኖን በዩሪያ ማከምና ድርቆሽ ሳይበላሽ የማቆየት ዘዴዎች ይገኙበታል ብለዋል፡፡ በሄክታር እስከ 50 ኩንታል ምርት ሊሰጡ የሚችሉ የቢራና የምግብ ገብስ፣ ባቄላና ሌሎች የሰብል ዝርያዎች የሚገኙ ሲሆን በብተናና በመስመር የመዝራት ልዩነትና ከዚሁም ሊገኝ የሚችሉ ጠቀሜታዎች መኖራቸውን ገልጸዋል፡፡ በንጥረ ምግብ ይዘት የበለፀጉ የደጋና የወይና ደጋ የጥራጥሬ ሰብሎችን በማምረት የቤተሰብ የንጥረ ምግብ አቅርቦትን ለማሻሻል፣ ናይትሮጂን ወደ ራሳቸው በማዋ