Posts

በጃፓን የኢፌዴሪ የክብር ቆንስላ ጽሕፈት ቤት ተከፈተ

Image
አዲስ አበባ፡- በጃፓን ናጎያ ከተማ የኢፌዴሪ የክብር ቆንስላ ጽሕፈት ቤት መከፈቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት ለጋዜጣው በላከው መግለጫ፤ ጽሕፈት ቤቱ በተከተፈበት ወቅት በጃፓን የኢፌዴሪ አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ «ኢትዮጵያ ነፃነቷን አስጠብቃ የቆየችና ለጥቁር ሕዝቦች ነፃነትና ፓን አፍሪካኒዝም የጐላ ሚና የተጫወተች ሀገር ናት» ማለታቸውን አስታውቋል። በአሁኑ ወቅትም ሠላምና መረጋጋት የሰፈነባት ከመሆኗም ባሻገር ልማቷን በማፋጠን ድህነትን ድል ለማድረግ እየተንቀሳቀሰች መሆኑ ተጠቁሟል። እንደ አምባሳደር ማርቆስ ገለጻ፤ የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ ያስቆጠረ ነው። ጃፓን በጠንካራ አጋርነቷ በተለይም የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪዎች ውጤታማነትን ከፍ በማድረግና በጐ ፈቃደኞችን በመላክ የቴክኒክና ዕውቀት ሽግግር እንዲስፋፋ አስተዋፅኦ እያበረከተች ነው። በጃፓን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ቪንቺ አሳዙማ በበኩላቸው፤ ጃፓንና ኢትዮጵያ ረጅም ጊዜ የቆየ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸው አመለክተው፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ሠላምና መረጋጋት እንዲሰፍን እያደረገች ያለው ጥረት የሚደነቅ መሆኑን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ በቀጣይ በምታዘጋጀው ለአፍሪካ ልማት የቶክዮ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይም ጠንካራ አስተዋፅኦ እንደሚኖራት ያላቸውን እምነት ጠቁመዋል። የክብር ቆንስላ ጽሕፈት ቤቱ መከፈት ሁለቱ አገራት ያላቸውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር የራሱ አስተዋፅኦ እንዳለው አመልክተዋል። በዕለቱ በጃፓን የኢትዮጵያ መንግሥት የክብር ቆንስላ ሆነው እንዲሠሩ የተመረጡት ሚስተር ላዲማቺ ማትሲሞት የሹመት ደብዳቤ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማን ከአምባሳደር ማርቆስ ተክሌ እጅ ተረክበዋል።

ብሄራዊ የስነ- ህዝብ ምክር ቤት ሊቋቋም ነው

Image
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 17፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) በያዝነው ዓመት የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር 84 ነጥብ 3 ሚሊዮን ገደማ መድረሱን ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ያደረገው ሳይንሳዊ ግምት ያመለክታል። የሃገሪቱ ፖሊሲ የህዝብ ቁጥርን መቀነስ ላይ ከማተኮር ይልቅ ፥ ያለውን የህዝብ ቁጥር ከሃገሪቱ የልማት አቅምና የኢኮኖሚ ክፍፍል ጋር ማጣጣም ላይ አተኩሮ የሚሰራ ነው። ኢትዮጵያም የህዝብ ቁጥሩን ዕድገት ከኢኮኖሚ ዕድገቷ ጋር ለማመጣጠን እንዲያስችላት ፥ ከዛሬ 18 ዓመት በፊት የስነ-ህዝብ ፖሊሲ ቀርጻ ወደ ትግበራ ብትገባም ፥ እስካሁን ተግባራዊ አልተደረገም። ይህንኑ የስነ-ህዝብ ጉዳይ የሚያስተባብረውን የብሄራዊ ስነ-ህዝብ ምክር ቤት ለማማቋም ፥ ባለፈው አመት ረቂቅ ደንብ በማዘጋጀት ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቅረቡን ፤ በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ተጠባባቂ የስነ-ህዝብ ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ መኮንን ናና ተናግረዋል። እሳቸው እንዳሉት የሚቋቋመው ምክር ቤት ይበልጥ ውጤታማ ይሆን ዘንድ ፥ እንደገና ሰፋ ያለ ጥናት ተደርጎበት ፤ በዚህ አመት መጨረሻ ወይም በሚቀጥለው አመት መጀመሪያ ላይ ፥ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ይቀርባል። ረቂቁ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ አስኪጸድቅ ድረስም ፥ የማስተባበሩን ሒደት ለማከናወን ሃገር አቀፍ ግብረ ሃይል በያዝነው ወር ውስጥ በማቋቋም ፥ ምክር ቤቱ እስኪመሰረት ግብረ ሃይሉ የማስተባበሩን ስራ እያከናወነ ይቆያል ብለዋል አቶ መኮንን። ሃገሪቱ ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ባለሁለት አሃዝ የኢኮኖሚ ዕድገት ብታስመዘግብም ፥ ካላት የህዝብ ብዛት ጋር መመጣጠን ባለመቻሉ አጠቃላይ የምርት መጠኗ 412 አሜሪካን ዶላር ላይ እንዲወሰን አስገድዷታል። የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ መረጃ እንደሚያመለክተው ደግሞ ፥ በሃገሪ

የሲኣን ምስረታ በኣል እና ኣዲስ ኣመራር

ከማህበራዊ መረብ ላይ የተገኘ  SLM (Sidama liberation movement) is transformed! Today is the day of transformation for SLM and/or Sidama As many sons, daughters and friends of Sidama have been writing and speaking in several medias, occasions, and moments the oppression, terrorism, and agony caused by the tyrant rulers of the past governments including the present one is immeasurable. Since the hands of occupiers had touched the land of Sidama, the people has been fighting and saying no to forceful occupation. Even after the consolidation of the power of the tyrants the people of Sidama hasn’t kept silent. Injustices and lack of good governance and basic human rights violations has been the concern of the entire Sidama. Today I am writing not to mention the injustices and immoral acts of the government.  I would like to take this opportunity to write little about today’s organized resistance response of our people. Of course our people had resisted the occupiers in an organized way incl

ተቃዋሚዎች ከኢህአዴግ ጋር ድርድር እንፈልጋለን አሉ

Image
በመጪው ግንቦት ወር በሚካሄደው የአካባቢና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ላይ ከመወያየታችን በፊት በምርጫው ዲሞክራሲያዊነትና ነፃ መሆን ላይ ልንወያይ ይገባል በሚል ለምርጫ ቦርድ በደብዳቤ ጥያቄ ያቀረቡ 34 ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ የምርጫ ምልክት ውሰዱ መባሉን ተቃወሙ፡፡ በምርጫ ቦርዱ ላይ እምነት ስለሌለን ከኢህአዴግ ጋር ያለቅድመ ሁኔታ ድርድር እንፈልጋለን ብለዋል - ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ፡፡የኢህአዴግ ጽ/ቤት ቢሮ ኃላፊና በጠ/ሚኒስትሩ የህዝብ አደረጃጀት አማካሪ አቶ ሬድዋን ሁሴን በበኩላቸው፤ የምርጫ ስነምግባር ደንቡን ካልፈረሙ ፓርቲዎች ጋር አንደራደርም ብለዋል፡፡  ፓርቲዎች የምርጫ ምልክታቸውን እስከፊታችን ሰኞ እንዲወስዱ ምርጫ ቦርድ ያስታወቀ ሲሆን ተቃዋሚዎች በበኩላቸው፤ ለቦርዱ ደብዳቤ በማስገባት ምላሽ እየጠበቁ ባሉበት ሰዓት የምርጫ ምልክት ውሰዱ መባላቸው አግባብ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡ ተቃዋሚዎች ላቀረቡት ጥያቄ ምርጫ ቦርድ “ምላሽ የሚሰጠው ተገቢ ጥያቄዎችን ሲያቀርቡ ነው” ሲል ለአዲስ አድማስ መግለፁ ይታወሳል፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ በቦርዱ ላይ እምነት እንደሌላቸው በመግለፅ፡- ከኢህአዴግ ጋር ውይይት እንደሚፈልጉና ከዛ በፊት የምርጫ ምልክት እንደማይወስዱ አስታውቀዋል፡፡ የመድረክ የስራ አስፈፃሚ አባልና የ34ቱ ፓርቲዎች ጊዜያዊ ኮሚቴ ዋና ሰብሳቢ አቶ አስራት ጣሴ ለአዲስ አድማስ ሲያስረዱ፤ “ከዚህ ቀደም የተደረጉ ምርጫዎች ችግር የነበረባቸው በመሆናቸው ከጊዜ ሰሌዳው በፊት በምርጫው ፍትሃዊነትና ዲሞክራሲያዊነት ላይ ውይይት እንዲደረግ ፒትሽን ተፈራርመን ለቦርዱ አስገብተን፣ ለሱ ምላሽ ሳይሰጥ ምልክት ውሰዱ መባሉ ተገቢ አይደለም” ብለዋል የምርጫ ቦርዱ ተአማኒነትና ተቀባይነት ጥያቄ ውስጥ ነው ያሉት አቶ አስራት ጣሴ፤ ከኢህአዴግ

የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ 35 ኣምስተኛውን የምስረታ በዓል በደማቅ ሁኔታ ኣከበረ፤ ኣዳዲስ የድርጅት ኣመራር መርጧል

የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ 35 ኣምስተኛውን የምስረታ በዓል በደማቅ ሁኔታ ኣከበረ፤ ኣዳዲስ የድርጅት ኣመራር መርጧል በዛሬው እለት በሃዋሳ ከተማ በዳግም ጂሚናዥዬም በተካሄደው የምስረታ  ሰነስርኣት ላይ የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ  35 ኣመት የምስረታ በኣል በተለያዩ  ዝግጅቶች ኣክብሯል። በርካታ የድርጅቱ ደጋፊዎች በተገኙበት በተካሄደው በዚህ ስነስርኣት ላይ ለሲዳማ ህዝብ ነጻነት ለተሰው ሰማዕታት የህልና ጸሎት የተደረገ  ሲሆን ድርጅቱን በቀጣይነት የምመሩ ኣመራሮች ተመርጠዋል። በኣጠቃላይ 15 ኣባላት ያሉት በኣብዛኛው ወጣቶችን የሆነና የዩኒቨርሲቲ ተማርዎችን ያቀፈ የድርጅት ኣመራር የተመረጠ ሲሆን ኣንጋፋ የሲዳማ ታጋዮችን በኣመራርነት ተካተዋል። በኣመራርነት ከተመረጡት መካከል ካላ ዋቃዮ፤ ዶክተር ኣለማዬሁ፤ እና ካላ ካሳ ኣዲሶ  ይገኙበታል። ክቡራን ኣንባቢያን  ዝርዝር ዜናውን እንደደረሰን እናቀርባለን