Posts

በሲዳማ ዞን ሎካ አባያ ወረዳ በየደረጃው ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሠራጨት ግብ ጥሎ እየሠራ መሆኑን የወረዳው ኦሞ ማክሮ ፋይናንስ ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በሲዳማ ዞን ሎካ አባያ ወረዳ በየደረጃው ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሠራጨት ግብ ጥሎ እየሠራ መሆኑን የወረዳው ኦሞ ማክሮ ፋይናንስ ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡ የንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ሀይለኢየሱስ እንደገለፁት መንግስት የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል በነደፈው ስትራቴጂ መሠረት በተያዘው በጀት ዓመት 1ዐ ሚሊዮን ብር ብድር ለማሰራጨት እና 18 ሚሊዮን ብር ከቁጠባ ለመሰብሰብ አቅዶ እየሰራ ነው፡፡ ንዑስ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ከንግድና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር ከተለያዩ ዩንቨርስቲዎችና ኮሌጆ  ለተመረቁ  ተማሪዎችን ከ5 መቶ ሺህ ብር በላይ የብድር አገልግሎት ለመስጠት ማቀዱን ገልፀዋል፡፡ በተያዘው እሩብ በጀት ዓመት 3 ሚሊዮን 6 መቶ ሺህ ብር ብድር ማሰራጨቱንና መቶ ሺህ ብር ቁጠባ መሰብሰብ መቻሉን ጠቁመው 6 ሺህ 8 መቶ የሚሆኑ የህብረተሰቡ ክፍሎች የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆናቸውን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል ሲል ሪፖርተር አካሉ ጥላሁን ከበንሳ ቅርንጫፍ ጣቢያ ዘግቧል፡፡

Human Rights Violations in Sidama, Southern Ethiopia

Appeal to:- Mr. Ban Ki -Moon, United Nation’s Secretary General, United Nations, 760 United Nations Plaza Manhattan, NY 10017, USA Mr. José Manuel Barroso President of the European Commission 1049 Brussels, Belgium Mrs. Inkosazana Dlamini Zuma, African Union’s Secretary General P.O. Box 3243 Roosvelt Street (Old Airport Area) W21K19 Addis Ababa, Ethiopia Secretary Hillary Rodham Clinton The US Department of State 2201 C Street Northwest Washington, DC, USA 20 November 2012 Subject: - Human Rights Violations in Sidama, Southern Ethiopia The Sidama people live in Southern Ethiopia. According to the Ethiopian Government’s official statistics, the current population of Sidama is 3.4 million (independent estimates suggest that the current total population is above 5 million). The Sidama nation had a long history, vibrant culture and democratic systems of governance based on traditional Kingships and various democratically elected traditional councils of elders. This traditional system of go

የህብረተሰብ ጤና ልማት ሰራዊትን ለመገንባት 63 ሺህ በላይ ሞዴል ቤተሰቦች ማፍራቱን የሀዋሣ ከተማ ጤና መምሪያ ገለፀ፡፡መምሪያው የ2ዐዐ5ሩብዓመትእቅድክንውንገምግሟል፡፡

Image
የእቅድ ክንውን ሪፖርት በቀረበበት ወቀት የመምሪያው ኃላፊ አቶ ደሰታ ዶጊሶ አንደተናገሩት በሩብ አመቱ የእናቶችንና የህፃናትን ሞት ለመቀነስ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ከከተማዋ ፈጣን እድገት ጋር ተያይዞ ሊከሰቱ የሚችሉ የጤናና የማህበራዊ ችግሮች በመፈታት ነዋሪውን ጤናማ፣ አምራችና የበለፀገ ለማድረግ የጤና ልማት ሰራዊት ግንባታ ተግባራዊ መሆን መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡ የህብረተሰብ ጤና ልማት ሰራዊትን ከመገንባት አንፃርም ከ63 ሺህ 993 ሞዴል ቤተሰቦች ማፍራቱን ተናግረዋል፡፡ በሪፖርቱ እንደቀረበው የሳንባ ነቀርሳ በሽታን መከላከያ ክትባት ለ2 ሺህ 678 ህፃናት ለመስጠት ታቅዶ 2 ሺህ 971 የተከናወነ ሲሆን ባለፈው ሩብ አመት አብዛኛዎቹ አፈፃፀሞች ከእቅዱ 9ዐ በመቶ እና ከዚያ በላይ ተግባራዊ መሆናቸው በሪፖርቱ ቀርቧል፡፡ ከመንጋጋ ቆልፍ በሽታ የተጠበቀ ህፃናት እንዲወለዱ ከማድረግ አንፃርም በሩብ አመቱ 2 ሺህ 678 ህፃናት አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ ከእቅድ በላይ መከናወኑንም ተጠቁሟል፡፡ በመቀጠልም በበጀት ዓመቱ የጤና ሴክተር ትኩረት የሚያደርገው የጤና ተቋማት በማስፋፋትና በግብዓት በሟሟላት የጤና አገልግሎቶች ጥረት ማሻሻል የእናቶችና የህፃናት ሞትን በመቀነስና ዋና ዋና ተላላፊ በሽታዎችና መከላከልና መቆጣጠር ላይ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ በጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች አማካኝነት 124 እናቶች የወሊድ አገልግሎት ለመስጠት እቅድ ተይዞ ለ49 እናቶች ብቻ አገልግሎት የተሰጠ ሲሆን በቀጣይም በተሻለ ሁኔታ ለመስራት ጥረት እንደሚያደርግ ተገልጿል፡፡ በምክክር መድረኩም የሀዋሣ ክፍለ ከተሞች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት የጤና ባለሙያዎች እና ሌሎች አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡http://www.smm.gov.et/_Text/1

የህፃናት መብቶችን በተመለከተ ከጊዜ ወደ ጊዜ የህብረተሰቡ ግንዛቤ እያደገ መምጣቱን በኢትዮጵያ ሠብአዊ መብት ኮሚሽን ሀዋሣ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ጽህፈት ቤቱ 7ኛውን የአለም ህፃናት ቀን ከትምህርት ቤቶች ጋር አክብ b ል፡፡ የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ አስተባባሪ አቶ አብርሃ አታሮ እንዳሉት ትምህርት ቤቶች ሰብአዊ መብትን በተመለከተ ህፃናት ተኮትኩተው የሚያድጉበት በመሆኑ የኮሚሽኑን አላማ ለማሳካት ትልቅ ፋይዳ አላቸው፡፡ መጪው ትውልድ ሰብአዊ መብቶችን ለማክበርና ለማስከበር የሚያስችለውን ስንቅ ከትምህርት ቤቶች ይቀስማል ብለዋል ፡፡ በሀገራችን ዘንድሮ ለ7ኛ ጊዜ የሚከበረው የዓለም ህፃናት ቀን “ሁሉም ህፃናት ሰብአዊ መብቶችን በማከበር፣ በማስከበርና ሌሎችንም በማስገንዘብ ትምህርት ቤቶች ትልቅ ሚና አላቸው” የሚል መርህ አላው፡፡ በበአሉ አለም አቀፍ የህፃናት መብቶች ኮንቬንሽንን፣ የአፍሪካ ህፃናት ሰብአዊ መብትንና የኢትዮጵያ መንግስት ለሠብአዊ መብቶች የሠጠውን ትኩረት የሚዳስስ ጽሑፍ ቀርቧል፡፡ የበአሉ ተሳታፊ ህፃናቶች የተለያዩ ጭውውቶችንና ሥነ ጽሑፎችን አቅርበዋል፡፡ ትምህርት ቤቶች በሥነ ምግባር የታነፀ የሞራል እሴት ያለው፣ የነቃና ህግ አስከባሪ ዜጋ ለመፍጠር የሚያደርጉትን ጥረት  ህብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት እንዲደግፉ ጥሪ ቀርቧል ፡፡ ባለደረባችን ደስታ ወ/ሰንበት እንደዘገበው፡፡http://www.smm.gov.et/_Text/11HidTextN305.html

ከመፈክር ይልቅ ዲሞክራሲ!

ሰላም! ሰላም! ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ላላችሁ በሙሉ። አንድ ወዳጄ ይኼንን የአቅጣጫ ሰላምታ እንደማይወደው አጫውቻችሁ አውቃለሁ? ለምንድን ነው ስለው ‹‹የሰው ልጅ እንደ ንፋስ በአቅጣጫ ላይ ተመሥርቶ ሰላምታ ሲለዋወጥ እበሽቃለሁ፤›› አይለኝ መሰላችሁ? የዘንድሮን ሰው የሚያበሽቀውን ነገር ብዛት ቆጥረን መጨረስ አቃተን! ግን ግን ንፋስን ለምንከተል የዘመኑ ሰዎች ይህ ሰላምታ ካልተሰጠ ለማን ይሰጥ? ለራስ ብቻ የሚሮጥበት ዘመን መሆኑን ካየን ዘንዳ ከዚህ ሌላ ምን ይባላል? አንዳችን ያለ ሌላችን መኖር እንደማንችል እያወቅነው ‘እኔ’ን ብቻ ላማከለ ነፍስ መሮጣችን ይገርመኛል። የሚገርማችሁ ደግሞ አባባልን እንኳ መርጠን አለመጠቀማችን ነው። ለምሳሌ ‹‹ዘመኑ የውድድር ነው›› የሚለውን አባባል ለተቀደሰ ይሁን ለረከሰ ተግባር እንደምንጠቀምበት ሳንለይ ለሁለቱም እንዳሻን እንገለገልበታለን። አሁንማ ሙሰኛውም በሰሞነኛ ተቆጣጣሪዎች ሲያላግጥ ‘ዘመኑ የውድድር ነው’ ማለት ጀምሯል አሉ። ‹‹ውድድሩ ጤናማ ዕድገት ለማስመዝገብ ነው? ወይስ እንደተለመደው ጠልፎ ለመጣል ነው?›› ይሉኝ ነበር ባሻዬ ይኼን ጉድ ቢሰሙ፡፡ ሌባ ቀጪ አጥቶ ለሕዝብ አገልግሎት በሚውል ገንዘብ ደልቦ ሲንጎማለል ይውላል። ተጠቂው ሰፊው ሕዝብ አቧራ ለብሶ ለዕለት ጉርሱ ይማስናል። ፍትሕ የናፈቃት ዓለም። በየጥጋጥጉ ዲስኩር ብቻ ተለጥፎ ይነበባል! ይነበነባል! የባሻዬ ልጅ፣ ‹‹አሁንማ የሰለቸኝ መፈክር ማንበብ ነው፤›› አለኝ፡፡ ‹‹ለምን?›› ብለው፣ ‹‹በመፈክር ውስጥ የተሸጎጡ በርካታ ውሸቶች አሉ፤›› ሲለኝ የገዛ ሳቄ ጆሮዬን አደነቆረው፡፡ ባለፈው ሰሞን አንድ የመንደራችን ጎበዝ ተማሪ ‹‹እኔ ከእንግዲህ ወዲያ ትምህርት የሚባል በቃኝ አቅለሸለሸኝ፤›› ብሎ አቆመው