Posts

ግልጽነትና ተጠያቂነት የመልካም አስተዳደር ወሳኝ መሣሪያዎች ናቸው

Image
ሕዝብም መልካም አስተዳደር እፈልጋለሁ ይላል፡፡ መንግሥትም መልካም አስተዳደርን ማስፈንና ማረጋገጥ ራዕዬ፣ ዓላማዬና ዕቅዴ ነው ይላል፡፡ በዚህ ላይ ልዩነት የለም፡፡ በአባባል፣  በፍላጎትና በምኞት ደረጃ፡፡ መልካም አስተዳደርን ተግባራዊ ለማድረግ ግን የግድ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን በተግባር ማስፈን ያስፈልጋል፡፡ ግልጽነትና ተጠያቂነት ከሌለ መልካም አስተዳደር አይኖርም፣ አይሰፍንም፡፡ ግልጽነት ሲባል ትርጉሙ ‹‹ግልጽና ግልጽ›› ነው፡፡ በሕዝብ ተመርጫለሁ የሚል መንግሥት ውክልና ሰጥቶ፣ መርጦ ለሥልጣን ላበቃው ሕዝብ የሚሠራውንና የሚያስበውን በግልጽ ማሳወቅ አለበት፡፡ ሕዝብ መንግሥትን እዚህ ጋ ተሳስተሃል፣ እዚህ ጋ አጥፍተሃል፣ እዚህ ጋ ጥሩ ሠርተሃል፣ እዚህ ጋ እንዲህ ብታደርግ ይሻላል በማለት ሕገ መንግሥቱ የሰጠውን መብት ተጠቅሞ ሐሳብ ለመስጠት፣ ሂስ ለማቅረብና ድጋፉን ለመግለጽ መንግሥት የሚያከናውነውን ሁሉ በግልጽ ሊያውቀው ይገባል፡፡ መንግሥት ግልጽ ሊሆንለት ይገባል፡፡ ሕገ መንግሥታችን ግልጽነትን ይደግፋል፡፡ ሁሉም ነገር ለሕዝብ ግልጽ እንዲሆን የሚያዝና የሚደነግግ ሕግም አለን፡፡ የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነፃነት አዋጅ፡፡ በሕገ መንግሥትና በሕግ በኩል በአገራችን ግልጽነት እንዳይኖር የሚያደርግ አንዳችም ነገር የለም፡፡ በተግባር ግን ግልጽነት እየተዳከመ ነው፡፡ በተግባር ግን ቢሮክራሲው የሚጠቅመውን ይናገራል፤ የማይጠቅመውንና የሚያጋልጠውን ይደብቃል እንጂ ግልጽነት (ትራንስፓረንሲ) እውን ሊሆን አልቻለም፡፡ ለመልካም አስተዳደር ትልቅ የተደቀነ እንቅፋት የሆነው የግልጽነት አለመኖር ሆኗል፡፡ ተጠያቂነትን (አካውንተቢሊቲ) በሚመለከትም ሕገ መንግሥታችንና ሕጎቻችን የሚደግፉትና የሚያበረታቱት ናቸው፡፡ በተግባር ግን ተጠያቂነት እየጠፋ ነው፡፡ ቢሮክራ

Media and the political process

The thinking that media and the political process have a dialectical relationship, that includes action and reaction, is a recent and not yet well developed theory of mass communication. Whether media actually does have the ability to influence foreign policy is the subject of intense debate among scholars, journalists and policy makers.  “The CNN (Cable News Network) Effect” , as it is called by scholars, however, demonstrates the impact of new global real time media. The CNN effect regards the role of media as typically substantial if not profound. Some radicals even define the CNN effect as a loss of policy control on the part of policymakers, because of the power of the media; a power that they can do nothing about. Their thinking is a major deviation from the existing and almost hegemonic thinking of the propaganda model. According to propaganda model the relationship between the media and the political process was seen as a rather supplementary one. The media were thought to

ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ውስጥ - የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽኗ እና የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ

Image
በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት መመረጥ ላይ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽነሯ እና የሰመጉ ዳይሬክተር ለቪኦኤ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ​​ የኢትዮጵያ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት አባልነት መመረጥ ካስመዘገበቻቸው የምጣኔ ኃብት እና ማኅበራዊ ስኬቶች በአካባቢውና በምክር ቤቱ ምሥረታ ላይም ከተጫወተቻቸው ሚናዎቿ ጋር የተያያዙ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር አምባሣደር ጥሩነህ ዜና አስታውቀዋል፡፡ የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ​​ በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫው በወቅቱ ያስደነገጠው መሆኑንና ምናልባትም ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች አያያዟን እንድታሻሽል ግፊት ማሣደሪያ አጋጣሚ ሊሆንም እንደሚችል የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ዋና ዳይሬክተር አቶ እንዳልካቸው ሞላ አመልክተዋል፡፡ ዝርዝሩን ከዘገባው ያዳምጡ፡፡ ዝርዝሩን ከዘገባው

የመልካም አስተዳደር ችግር -ያልተሻገርነው የዕድገት ማነቆ

ብሩክታይት ፀጋዬ በእኛ ሀገር በአንድ ወቅት ደመቅ በሌላ ጊዜ ደግሞ ድብዝዝ የሚሉ ጉዳዮች በርካታ ናቸው፡፡ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ስለተናገሩትና በመገናኛ ብዙሃን ስለ ተቀባበሉት ብቻ ሞቅ የሚሉ ጉዳዮች በርካታ ናቸው፡፡ አንዳንዴ ሞቅታው በቃላት ብቻ ሳይሆን በተግባርም ይገለጻል፡፡ ከእነዚህ አንድ ወቅት ያዝ ሌላ ጊዜ ደግሞ ለቀቅ ከምናደርጋቸው ብዙ ጉዳዮች አንዱ የመልካም አስተዳደር ጉዳይ ነው፡፡ በአንድ ወቅት ስለ መልካም አስተዳደር ብዙ ብዙ ተባለ፡፡ በእርግጥ ይህ ጊዜ ማን አገልጋይ ማን ደግሞ ተገልጋይ እንደሆነ ጥርት ያለ ግንዛቤ የተያዘበትና በመልካም አስተዳደር ረገድ አንድ ወሳኝ ምዕራፍ የተሸጋገርንበት በመሆኑ ጉዳዩ መነሳቱ በራሱ መልካም ነገር ነው ማለት ይቻላል፡፡ ጉዳዩ በመነሳቱ «ደንበኛ ንጉሥ ነው» አመለካከትን ለማዳበርም ተችሎ ነበር፡፡ የዛሬን አያድ ርገውና፡፡ «የት መሄድ ይፈልጋሉ?»ከሚለው አቅጣጫ ጠቋሚ ጀምሮ የሠራተኞችን ስም በየቢሮው በር ላይ መለጠፍና ባጅ እንዲያን ጠለጥሉ እስከማድረግ፣የቅሬታ ሰሚ አካላት በማቋቋም ተጠያቂነት ያለው አሠራር እስከማስፈን እሰየው የሚያሰኙ በጐ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ከዓመታት በፊት የተተከሉት የአስተሳሰብና የአሠራር ሥርዓቶች አሁንም ቀጥለውና ተጠናክረው የሚተገበሩባቸው ተቋማት እንዳሉ ሁሉ እነዚህ የሕዝብ አገል ጋይነት መገለጫዎች ለሙሰኞችና ለመልካም አስተዳደር ጠንቆች ሽፋን ሲሰጡም ተመል ክተናል፡፡ ተጠቃሚዎችን በአግባቡ ማስተናገድ ዓላማቸው አድርገው ከሚንቀሳቀሱ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ዓይነት ተቋማት እንዳሉ ሁሉ አንዴ መልካም ሌላ ጊዜ ደካማ አፈፃፀም እያሳዩ በአንድ ወቅት ደመቅ ብለው ሌላ ጊዜ ደግሞ ሸርተት ሲሉ የምናያቸው ተቋማትም መኖራቸው የማይካድ ነው፡፡ ሌሎቹ ደግሞ የ

የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ በኦሮሚያና በደቡብ ክልሎች በ1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወጪ የርብና ጊዳቦ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እያካሄደ መሆኑን ገለጸ።

Image
አዲስ አበባ ህዳር 09/2005 የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ በኦሮሚያና በደቡብ ክልሎች በ1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወጪ የርብና ጊዳቦ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ እያካሄደ መሆኑን ገለጸ። ግንባታው ሲጠናቀቅ 26 ሺህ ሄክታር የሚደርስ የመስኖ መሬትን ማልማት እንደሚያስችል ተገልጿል። የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ አስተማማኝ የውኃ አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል የርብና የጊዳቦ መስኖ ልማት ፕሮጀክቶች የግድብ ግንባታ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በደቡብ ጎንደር ዞን በእብናትና ፋርጣ ወረዳዎች እንዲሁም በፎገራ ሜዳማ አካባቢ የሚገነባው የርብ ግድብ 234 ሜትር ኩብ ውኃ የመያዝ አቅም እንዳለው ገልጸዋል፡፡ የግድቡ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ 14 ሺህ ሄክታር መሬት በመስኖ የማልማት አቅም የሚኖረው ሲሆን ከ28 ሺህ በላይ አባዎራዎቸን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ በግድቡ ግንባታ ወቅት 400 ለሚደርሱ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር የታቸለ ሲሆን ከዚህም ውስጥ 75 ያህሉ ሴቶች መሆናቸውን ተናግረዋል። የርብ ግድብ ግንባታ አጠቃላይ ወጪ 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ የግድቡ ግንባታ በያዝነው ዓመት ሰኔ ወር እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋዕል፡፡ በተመሳሳይም በኦሮሚያና በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ሕዝቦች ክልሎች በሲዳማና ቦረና ዞን አዋሳኝ በሚገኙ ዓባያና ለኮዓባያ ወረዳዎች 117 ነጥብ 8 ሚሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ የመያዝ አቅም ያለው የጊዳቦ የመስኖ ልማት ግድብ ፕሮጀክት በመገንባት ላይ እንደሚገኝ አቶ ብዙነህ አመልክተዋል፡፡ የግድቡ ግንባታ ሲጠናቀቅ 11 ሺህ 924 ሄክታር ማልማት የሚያስችል ሲሆን ከ79 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍልን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አስረ