የኢትዮጵያ ፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት ወደ ግብፅ ሊጓዙ ነው
በዮሐንስ አንበርብር ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ አባላትን ያካተተ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥትን በመወከል፣ ኢትዮጵያ የምትገነባው ታላቁ የህዳሴ ግድብ በዓባይ ወንዝ ላይ ምንም ጉዳት የሚያስከትል መሆኑን ለማስረዳት፣ የኢትዮጵያንና የግብፅን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከር የሚል ተልዕኮ ይዞ ወደ ግብፅ ሊያቀና ነው፡፡ የዲፕሎማሲ ቡድኑ አባላት ከዩኒቨርሲቲ ምሁራን፣ ከታዋቂ ሰዎች፣ ከመገናኛ ብዙኅን፣ ከሥነ ጥበብና ከእምነት መሪዎች የተውጣጡ ሲሆን፣ በትናንትናው ዕለትም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተገኝተው በተጠባባቂ ማኒስትሩ አምባሳደር ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ ገለጻ ተደርጐላቸዋል፡፡ ኢትዮጵያና ግብፅ የረዥም ዘመናት ግንኙነት ያላቸው አገሮች መሆናቸውን በመጥቀስ ገለጻቸውን የጀመሩት ተጠባባቂ ሚኒስትሩ፣ ይህ ግንኙነታቸው ከተፈጥሮና ከመንፈሳዊ እምነት ጋር የተዛመደ እንደሆነ አስታውሰዋል፡፡ በዚህ ረጅም ዘመን የሁለቱን አገሮች ግንኙነት የሚያስተሳስሩ በርካታ መልካም ነገሮች የመኖራቸውን ያህል፣ በተለያዩ ጊዜያት የተከሰቱ የፖለቲካ መሪዎችም ግንኙነታቸውን ሲያሻክሩና ጠባሳ ለመፍጠር ሲሞክሩ እንደነበር አስረድተዋል፡፡ ኢሕአዴግ ሥልጣን ከያዘ በኋላ ግን ሁለቱ አገሮች ከዚህ ቀደም የነበራቸውን አለመግባባት ለመቅረፍ ጥረት መደረጉን የገለጹት ተጠባባቂ ሚኒስትሩ አምባሳደር ብርሃነ፣ እ.ኤ.አ. በ1993 የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ወደ ግብፅ በመሄድ የሥራ ጉብኝት ያደረጉ መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ በዚህ ወቅትም አቶ መለስ መንግሥታቸው በዓባይ ጉዳይ ላይ መወያየትን እንደሚፈልግ በመግለጻቸው፣ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የሁለቱ አገሮች ውይይት እንደተጀመረና በከፍተኛ ሁኔታ እንዳደገ ገልጸዋል፡፡ በመሆኑም ግብፆች ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ