Posts

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በይርጋዓለም ከተማ አዲስ ካምፓስ ከፈተ

Image
ሀዋሳ (ኢዜአ)፦ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የቅበላ አቅሙን ለማሳደግ በይርጋዓለም ከተማ በ55 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው አዲሱ የአዋሳ ካምፓስ ትናንት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ ካምፓሱን መርቀው የከፈቱት የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የዩኒቪርሲቲው አስተዳደር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ናቸው፡፡ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ እንደገለጹት፤ የዩኒቨርሲቲውን የቅበላ አቅም ለማሳደግ ከሚካሄዱ የማስፋፊያ ግንባታዎች አንዱ አካል የሆነው አዲሱ የአዋሳ ካምፓስ በ65 ሄክታር ቦታ ላይ ያረፈ ነው፡፡ በ2002 ዓ.ም ተጀምሮ በአሁኑ ወቅት የተጠናቀቀው ይኸው ካምፓስ ለ800 ተማሪዎች የመኝታ አገልግሎት የሚሰጥ ዘመናዊ ህንፃ ፣ የመማሪያና ሌሎችም ክፍሎችን የያዘ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ካምፓሱ በአሁኑ ወቅት በአካውንቲንግ፣ በማኔጅመንት፣ በኢኮኖሚክስና፣ በኮፕሬቲቭስ ዘርፍ በመጀመሪያ ዲግሪ የተቀበላቸውን 580 ተማሪዎችን በመመዝገብ ለማስተማር መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም በዚሁ አዲስ ካምፓስ በ38 ሚሊዮን ብር ወጪ የተጀመሩ የአስተዳደር ቢሮዎች፣ የተማሪዎች መመገቢያ፣ ቤተመጻሕፍትና የመምህራን መኖሪያ ግንባታ በቅርቡ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ዶክተር ዮሴፍ አመልክተው፤ የካምፓሱን የቅበላ አቅም በማገናዘብ ሌሎች የማስፋፊያ ግንባታዎች ለማካሄድ 320 ሚሊዮን ብር መመደቡን ጠቁመዋል፡፡ አዲሱን ካምፓስ እንዲከፈት ድጋፍ ላደረጉ ለክልሉ፣ ለሲዳማ ዞን፣ ለዳሌ ወረዳና ለይርጋዓለም ከተማ አስተዳደር፣ ለአካባቢው ማህበረሰብና ለሌሎችም ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡  የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እና የዩኒቨርሲቲው ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ካምፓሱን መርቀው ከከፈቱ በኋላ እንደ

አካል ጉዳተኞችን በማቋቋምና በመደገፍ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ማብቃት በሚል የክልሉ አካል ጉዳተኞች ማህበር ያዘጋጀው የኘሮጀክት ትውውቅ መድረክ በአለታ ወንዶ ወረዳ ተካሄደ፡፡

አቶ ባልጉዳ ጳውሎስ የአለታ ወንዶ ወረዳ አካል ጉዳተኞች ማህበር ሊቀመንበር እንዳሉት አካል ጉዳተኞች ካለባቸው ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ተላቀው የበኩላቸውን  አስተዋፅኦ ለማበርከት የልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የባለ ድርሻ አካላት ድጋፍና ትብብር ወሳኝ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ አቶ ተፈራ ጨመሳ የክልሉ አካል ጉዳተኞች ማህበር አማካሪ በበኩላቸው አካል ጉዳተኛችን ለማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ልማት ከማብቃት በተጨማሪ የአካል ጉዳተኛ ህፃናትን የትምህርት ተሳትፎ በማሳደግ የወደፊቱን የትውልድ ተስፋ እንዲያብብ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለአስሩ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ለእያንዳንዱ ተማሪ በወር 15ዐ ብር ለአስር ወራት ድጋፍ በማድረግ ለሁሉም ተማሪዎች 15 ሺህ ብር ተመድቦላቸው በመማር ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን እንደዘገበው፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/02HidTextN405.html

ባለፈው ዓመት በሁሉም የልማት እቅዶች አፈፃፀም ላይ የታዩ ክፍተቶችንና ውስንነቶችን ለመቅረፍ መዘጋጀቱን በሲዳማ ዞን የቡርሳ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ፡፡

የወረዳው ምክር ቤት 3ኛ ዙር 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ሲካሄድ ዋና አስተደደሪው አቶ አማረ ሻላሞ እንዳሉት  የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ለማሳካት ሁሉም የልማት እቅዶች በጠንካራና በተደራጀ የልማት ሰራዊት መመራት አለባቸው ብለዋል፡፡ በወረዳው በሚከናወነው የበልግና የመኸር እርሻ 7 ሺህ 831 ሄክታር መሬት በዋና ዋና ሰብሎች በመሸፈን 16 ሺህ 584 ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልፀዋል፡፡ ለዚህም15 ሺህ 13ዐ ኩንታል ዳኘና ዩሪያ ማዳበሪያ እንዲሁም አሲዳማ አፈርን በማከም ለእርሻ ሥራ ለማዋል 2ዐዐ ኩንታል ኖራና የተለያዩ ሰብሎች 3 ሺህ 289 ኩንታል ምርጥ ዘር በግብዓትነት እንደሚሠራጭም አቶ አማረ አስረድተዋል፡፡ ጉባኤው ከ39 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በማፅደቅ መጠናቀቁንም የሲዳማ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን መምሪያ ዘግቧል፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/02HidTextN505.html

የሲዳማ ሕዝብ መሠረታዊ ጥያቄ

በ Hagerselam Haroressa ከማህበራዊ መረብ ላይ የተገኘ ጽሁፍ የሲዳማ ሕዝብ መሠረታዊ ጥያቄ መግቢያ አገራችን ለአያሌ ዘመናት ለተለያዩ ሰው ሠራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ተጋልጣ የቆየች በመሆኗ አብዛኛው ህዝቧ በድህነት አረንቋና በኋላቀርነት ቀንበር ተተብትቦ መኖሩ የማይካድ ታሪካዊ ሀቅ ነው :: የሲዳማ ህዝብም የዚሁ አስከፊ ሰቆቃ ተጠቂ በመሆኑ ይህንን ነባራዊ ችግር ለመታገልና ለመፍታት ፈርጀ - ብዙ ትግል ማድረግ በማስፈለጉ፣ እንዲሁም የችግሩን መሠረታዊ ምንጭ አጉልቶ ለማሳየትና የመፍትሔውንም አቅጣጫ ለመጠቆም የሚያስችል የትግል ስልት ያካተተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ጽሑፍ ለ ማዘጋጀት ተገደናል :: እንደሚታወቀው የሲዳማ ብሔር ባለፉት አፋኝ ፀረ - ዲሞክራሲያዊ ሥርዓቶች ሥር ከመውደቁ በፊት የራሱ የሆነ ባሕላዊ የአስተዳደር ሥርዓት (The Luwa System) ፣ ቋንቋና (Sidaamu Afoo) ባህል፣ የራሱ የሆነ ታሪካዊ አመጣጥ ያለው ህዝብ ሆኖ በአንድ ጆኦግራፊያዊ ክልል ሰፍሮ የሚኖር በአንድ ስነልቦና የተሳሰረ ታላቅ ብሔር እንደሆነ ይታወቃል :: ይሁን እንጂ ህዝቡ በእነዚያ አስከፊና አፋኝ ፀረ - ዲሞክራሲያዊ ሥርዓቶች ሥር ከወደቀ በኋላ በራሱ ማስተዳደር እንዳይችልና ነፃነት እንዳይኖረው ፣ በገዛ ክልሉ ሊኮራባቸው ቀርቶ በአደባባይ በቋንቋውና በባህሉ እንዳይጠቀምበት ይልቁንም እንዲያፍርበት ተደርጎ ቆይቷል ::  በአጠቃላይ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ልማት የበላይ ባለቤትነትና ተጠቃሚነት እንዳይኖረው በተለያዩ ሥውር ስልቶች ተከልክሎ ቆይቷል :: ከእነዚህ አስከፊና አፋኝ ፀረ - ዲሞክራሲያዊ ሥርዓቶች ለመላቀቅ በየሥርዓቱ በተናጠል፣ በቡድንና በተደራጀ መልኩ ሳይታገል ያለፈበት አንድም ጊዜ አልነበረም :: በተለይ የንጉሣዊው ሥርዓ