34 ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫው ፍትሃዊነት ላይ ጥያቄ አለን አሉ
ኢህአዴግ ሚዲያውን ለምርጫ ቅስቀሣም ሆነ ፖሊሲውን በስፋት ለህዝቡ ለማድረስ እየተጠቀመበት እንደሆነና በፓርቲው ንብረትና በኢትዮጵያ ህዝብ ንብረት መካከል ያለው ልዩነት እንደማይታወቅ በመግለፅ ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ የሚያቀርቡትን አቤቱታ ተቀባይነት የለውም ያሉት ኃላፊው፤ ህዝቡ ኢህአዴግን መንግስት አድርጐ ሲመርጥ ፖሊሲውን በስፋት እንዲያስተዋውቅ እውቅናና ይሁንታ ሰጥቶታል ብለዋል፡፡ በተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚቀርቡትን ቅሬታና አቤቱታዎች በጋራ ምክር ቤት እያዩ መፍትሔ እንደሚፈልጉና በተባለው ጉዳይ ግን የቀረበላቸው አንዳችም ቅሬታ አለመኖሩን አቶ ተመስገን ጨምረው ገልፀዋል፡፡ የምርጫ ሥነ ምግባር ህግ ከፈረማችሁ በኋላ የዚህ ዓይነት ጥያቄ ማቅረብ የሥነ ምግባር ህጉን እንደመጣስ አያስቆጥራችሁም ወይ ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ፤ በ2002 ዓ.ም ምርጫው በተካሄደ በ3ኛው ቀን ኢህአዴግ በምርጫው ማሸነፉን በመግለፅ የምርጫ ሥነ ምግባሩን በግንባር ቀደምትነት ጥሶታል ብለዋል፡፡ የምርጫ ቦርድ ለጥያቄያቸው ተገቢ ምላሽ ካልሰጣቸው ሰላማዊና እርምጃ እንወስዳለን ይህ እርምጃም ሰላማዊ ሰልፍን ጨምሮ ህዝባዊ ንቅናቄ እስከመፍጠር የሚደርስ ነው ሲሉም አክለዋል፡፡ የምርጫ ቦርድ የህዝብ ግንኙነት ማስተባበሪያ ኃላፊ ወ/ሮ የሺ ፈቃድ፤ ፓርቲዎቹ ስላቀረቡት ጥያቄ የሚያውቁት ነገር አለመኖሩን ገልፀው፣ ጥያቄያቸው በቦርድ የሚፈታና አግባብነት ያለው ከሆነ በወቅቱ ምላሽ እንደሚሰጧቸው ተናግረዋል፡፡ ቦርዱ ለገዥው ፓርቲ የሚያዳላና ገለልተኛ አይደለም በማለት ፓርቲዎቹ ያቀረቡትን አቤቱታ አስመልክቶ ሲናገሩም የ2002 ምርጫ ሲጠናቀቅ ቦርዱ አዘጋጅቶት በነበረው የምርጫ ግምገማ መድረክን ጨምሮ ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ በቦርዱ ቅሬታ እንደሌላቸው ተናግረዋል፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የዚህ አይነት ቅሬታ የሚያ