''ኢትዮጵያ ከቡናው ዘርፍ ለማግኘት ያሰበችውን ገቢ ለማሳካት ጥረቷን አጠናክራ ትቀጥላለች''-ጠ/ሚ ኃይለ ማርያም
አዲስ አበባ ጥቅምት 29/2005 ኢትዮጵያ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዷ ከቡናው ዘርፍ ለማግኘት ያሰበችውን ገቢ ለማሳካት ጥረቷን አጠናክራ እንደምትቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ የመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ የቡና ጉባዔ ሲከፍቱ እንደተናገሩት አገሪቱ ከዘርፉ እያገኘች ያለችውን ገቢ በይበልጥ በማሳደግ የኢኮኖሚዋን ዕድገት ለማስቀጠል እንቅስቃሴዋን ታጠናክራለች። ኢትዮጵያ ባለፉት አራት ዓመታት በዓይነቱ በአፍሪካ የመጀመሪያ በሆነው በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል በማገበያየት የተሻለ ገቢ እያገኘች መሆኗንና ከቡና የተገኘው ገቢ ከአጠቃላይ የአገሪቱ ገቢ 74 በመቶ መድረሱን አስታውቀዋል። በዚህም እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠርበ2010/11 የምርት ዘመን ባቀረበችው ምርት ከ235ሺህ ቶን በላይ ቡና በማቅረብ 768ነጥብ 8 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ተናግረዋል። ባለፉት ዘጠኝ ዓመታትም በአማካይ 200ሺህ ቶን ቡና ለዓለም ገበያ በማቅረብ 842ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገቢ ስታገኝ መቆየቷንም አስታውሰዋል። አገሪቱ ለቡና ምርት ባላት አመቺነት ከአንድ ሚሊዮን በላይ አርሶ አደሮች በምርታማነትና ከ15ሚሊዮን በላይ በቀጥታና በተዘዋዋሪ በምርት ሂደቱ ላይ መሰማራታቸውን ገልጸው፣ከዘርፉ ልማት በይበልጥ የምትጠቀምበትን ሁኔታ ለመፍጠር ጥረቱ እንደማይቋረጥም አቶ ኃይለማርያም አረጋግጠዋል። የጉባዔው ተሳታፊዎች የአገሪቱን ቡና ምርታማነት ለማሳደግ የሚደረገውን እንቅስቃሴ በማገዝ በዘርፉ ያሉትን ችግሮች በመለየት ፍሬያማ ውጤት እንደሚያስገኙም ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም እምነታቸውን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ ኮፊ ኤክስፖርተርስ አሶሴሽን የቦርድ ሊቀመንበር አቶ ሁሴን አግራው በበኩላቸው