Posts

ኢትዮጵያ የንቅናቄውን 15ኛ ዓለም ዓቀፍ ጉባዔ ከጥቅምት 12 ጀምሮ ታስተናግዳለች

Image
አዲስ አበባ ጥቅምት 10/2005 ኢትዮጵያ 15ኛውን የትብብር ለታዳጊ ከተሞችና ልማት ንቅናቄ(ኮዳቱ)ን ዓለም ዓቀፍ ጉባዔን ለማስተናገድ ዝግጅቷን ማጠናቀቋን የጉባዔው ዝግጅት ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከድርጅቱ ጋር በመተባበር ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ለአራት ቀናት በአዲሱ የአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ " የከተሞች ጉዞ ለከተሞች አደረጃጀትና እድገት" በሚል መሪ ቃል ይካሄዳል፡፡ የኮሚቴው ሰብሳቢና የአንበሳ የከተማ አውቶቡስ አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ በድሉ አሰፋ ዝግጅቱን አስመልክቶ ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት ጉባዔው በከተማዋ የሚካሄደውን ፈጣን የለውጥ ጉዞ አጠናክሮ ለመቀጠል ያግዛል፡፡ ጉባዔው በከተማዋ በትራንስፖርት ዘርፍ ያለውን ዕድገት፣ ተሞክሮዎችንና አማራጮችን ለአገሪቷ በሚስማማ ሁኔታ ለመጠቀም እንደሚያስችልም አስረድተዋል። በጉባዔው ላይ ከ600 በላይ የከተሞች የትራንስፖርት አመራር አባላትና ባለሀብቶች እንደሚሳተፉበትና ከዚህ ወስጥ ከ250በላይ የሚሆኑት የአገር ውስጥ ተሳታፊዎች እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ እንዲሁም የከተማዋን እምቅ የኢንቨስትመንትና የንግድ አማራጮችን ለማስተዋወቅና የቱሪዝም መስህቦችን ለማስተዋቅ መልካም ዕድል እንደሚፈጥርም ሰብሳቢው ገልጸዋል፡፡ በጉባዔው ላይ የ30 አገሮች ተጨባጭ ተሞክሮዎች ይቀርባሉ ያሉት ሰብሳቢው፣በዚህም የሌሎች አገሮችን ልምድ ለመቅሰም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው አስረድተዋል፡፡ የጉባዔው ተሳታፊዎች አገሪቱን ለማወቅ የሚያስችላቸው ድረ ገጽ መከፈቱንና የትራንስፖርት አገልግሎት መዘጋጀቱን አቶ በድሉ ተናግረዋል፡፡ እንዲሁም በእንግሊዝኛና በፈረንሳይና ቋንቋዎች ትርጉምና መረጃ በመስጠትና በማስተላለፍ በኩል ሁለገብ አገልግሎት የሚሰጡ ወጣት ባለሙያዎች መዘጋጀታቸው

የሲዳማ ኣርነት ግንባር ሊቀመንበር ካላ ቤታና ሆጤሳ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከሰይፌ ነበልባል ሬዲዮ ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ

Image
ከካላ ቤታና ሆጤሳ ጋር የተደረገውን ቃለ ምልልስ ከ5 ደቂቃ ጀምሮ  ይከታተሉ።

ጉዞ ኃይለ ማርያም - ከአረካ እስከ አራት ኪሎ

Image
በዮናስ አብይ የ43 ዓመቱ ጐልማሳ መንገሻ መንዳዶ የተወለደባትንና አድጐ የተማረባትን አነስተኛዋን የአረካ ከተማን ለቆ መኖርያውን በአርባ ምንጭ ከተማ ካደረገ ከሁለት አሥርት ዓመታት በላይ አስቆጥሯል፡፡ ዛሬ የሥራ ጠባዩ በፈጠረለት አጋጣሚ ሙሉ ጊዜውንና ኑሮውን በአርባ ምንጭ ላይ በመመሥረቱ አልፎ አልፎ በአዕምሮው ውልብ ከሚሉበት ትዝታዎች በስተቀር ስለተወለደባት የአረካ ከተማ ሲያወሳ አይሰማም፡፡ ነገር ግን ስለተወለደባት ከተማ ከማይረሳቸው የልጅነት ትውስታዎቹ ውስጥ አንድ አስገራሚ ታሪክን ከተማሪነት ዘመኑ መዝዞ በፈገግታና ኩራት በተሞላበት ሁኔታ ሲያወጋ፣ ያድማጭን ጆሮ በጉጉት ሊያቆም እንደሚችል በቅድሚያ ከገጽታው ደማቅነት መረዳት ይቻላል፡፡ የታሪኩ ክስተት ወደኋላ 28 ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ 300 ኪሎ ሜትር በምትርቀው በአረካ ከተማና በነዋሪዎቿ ታላቅ የመደነቅ ስሜትን ስለፈጠረ  የአንድ ጎበዝ ተማሪን አስደናቂ ጉዳይ ያወሳል፡፡ መንገሻ በወቅቱ ከሚማርበት የአረካ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይልቅ ከከተማዋ ዕምብርት ሦስት ኪሎ ሜትር ርቀት ስለሚገኘው ዱቦ የካቶሊክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ስላለ አንድ ተማሪ ጉብዝና መስማትና ማውራት ይመስጠው ነበር፡፡ “በዚያ የሕፃንነት ዕድሜ ሁሉም ሰው ስለሱ ጉብዝና ብቻ ሲወራ ትዝ ይለኛል፡፡ እኔም በእኛ ትምህርት ቤት ውስጥ ካሉ ጐበዝ ተማሪዎች ይልቅ በዚያኛው ትምህርት ቤት ስላለው ጐበዝ ተማሪ ብሰማም ባወራም አልጠግም ነበር፤” በማለት የሚናገረው መንገሻ አገለለጹና ገጽታው ይህ ታሪክ እንኳን 28 ዓመታት ቀርቶ አሥር ዓመት የሞላው አይመስልም፡፡ በነዚያ ዘመናት ውስጥ እነ መንገሻ ከሚኖሩበት ከተማ አልፎ በድፍን ቦሎሶ ሶሬ በጉብዝናውና በቀለም ትምህርት አያያዙ “ያሳድግህ” ተብሎ

የሲዳማ የፖለቲካ ፓርቲዎች

ከታዛቢው ሲኣን በሲዳማ ጉዳዮች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ከመስጠት ያለፈ ስራ ስሰራ ኣይታይም የሲዳማ ዲያስፖራ የፖለቲካ ድርጅቶች የኢንተርኔት ላይ ኣንበሶች ናቸው ይሄ ቀጥዬ የማቀረበው ኣስተያየት የእኔ የግሌ ኣስተያየት ነው። ምናልባት በእኔ ማንነት ላይ ጥርጣሬ ቢኖር እኔ የመንግስት ደጋፊ ወይም ተቃዋሚም ኣይደለሁ፤ እንዲሁም የተቃዋሚዎች ደጋፊም ሆነ የተቃዋሚዎች ተቃዋሚም ኣይደለሁ። እኔ የሲዳም ህዝብ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መብቶች ስከበሩ ማየት የምሻ የሲዳማ ህዝብ ተቆርቋር ነኝ። እባካችሁ ከዚህ ባለፈ ሌላ ስም ኣትለጥፉብኝ ኣደራ። ስለ እራሴ ይህንን ያህል ካልኩ ወደ ጉዳዬ ልለፍ፦ በተለይ ካለፉት ሶስት ወራት ወዲህ ሲዳማ በፖለቲካ ትኩሳት ውስጥ ናት ማለት ይቻላል። በተለይ ከክልል ጥያቄ እና ከሃዋሳ ከተማ የወደፊት እጣ ፋንታ በምወሰኑ ጉዳዮች ላይ ህዝቡ ከመንግስት ጋር ተፋጦ መክረሙ ይታወሳል። ታዲያ ይህ ፍጥጫ ከፍጥጫነት ኣልፎ ወይም ኣፍትልኮ የወጣበትም ኣጋጣም ተከስቶ ነበረ በተለይ በወረዳዎች ኣከባቢ። የሆነ ሆኖ ዛሬ ግን ፍጥጫው እየረገበ ያለ ይመስላል። ይህንን ያነሳሁት ያለፈ ታሪክ ልተርክላችሁ ብዬ ኣይደለም፤ ያነሳሁበት ዋናው ምክንያት ስለ ሲዳማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የታዘብኩትን ጀባ ልላችሁ ብየ ነው። ምን ታዘብክ ብላችሁ ጠይቁኝ ታዲያ ! ኣዎን የሲዳማ የፖለቲካ ድርጅቶችን ብዙ እየታዘብኩ ነው። ለመሆኑ የሲዳማ የፖለቲካ ፓርቲዎች እነማናቸው ? ይመስለኛል ስለ ፓርቲዎቹ ማውራታችን ካልቀረ ስለ ማንነታቸው በስሱ ማንሳቱ የግድ ይመስለኛል። እኔ ከልጅነተ ጀምሮ የማውቀው ኣንዳንዴ ስለው ተቃዋሚ ስለው ደግሞ የመንግስት ደጋፊ እየሆነ ሁለት መልክ የሚይዘው የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ( ሲኣን ) ከቀድሞው ሲ

በሲዳማ ዞን የአማራጭ ኢነርጂ ልማት በመጠናከር ላይ ነው

Image
ሰሞኑን በሃዋሳ ከተማ በተካሄደው የደቡብ ክልል የውሃ ጉባኤ የቀረበው የ 2004 ኣ / ም የመምሪያው የስራ ኣፈጻጸም የተመለከተው ኣንድሪፖርት እንዳመለከተው በዞኑ ውስጥ በኣማራጭ ኢነርጂ ልማት ዘርፍ ኣበራታች ስራዎች ተከናውነዋል። መምሪያው በባጀት ኣመቱ ለማከናወን ካቀዳቸው 19 አዲስ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃ አምራቾች ማህበራት እንዲቋቋሙ በማድረግ ለ 3- ማህበራት ፕሬስና ሞልድ ተገዝቶ ድጋፍ ማድረጉ የተገለጸ ሲሆን፤ በ 19 ወረዳዎች በ 38 አማካይ ቦታዎች የማገዶ ቆጣቢ ምድጃ ላይ ለሕ ብረተ ሰቡ ግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት በመስጠት ከእቅዱ በላይ በመስራት 4500 የተሻሻሉ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎ አንዲሰራጩ በማድረግ በርካታ የዞኑን ነዋሪዎች ተጠቃሚ  ኣድርጓል ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በሁሉም ወረዳዎች 100 የሚሆኑ የቤተሰብ የሶላር ተጠቃሚ ማህበራት መደራጀታቸው ሲገለጽ፤ የኃይል አማራጭ ኢነርጂ አጠቃቀም ላይ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል። እንደሪፖርቱ ከሆነ የሶላር ኢነርጂ ተከላ እና የባዮ ጋዝ ግንባታ በተለያዩ ወረዳዎች የተካሄደ ሲሆን፤ ኣራት የአማራጭ ኢነርጂ ዳሰሳ ጥናት ም ተከናውነዋል።