መንግሥት ባከናወናቸው ተግባራት የዋጋ ግሽበቱ ወደ 19 በመቶ ዝቅ ማለቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ገለጹ
አዲስ አበባ ጥቅምት 6/2005 መንግሥት የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ባከናወናቸው ተግባራት ባለፈው ዓመት የዋጋ ግሽበቱ ከ40 በመቶ ወደ 19 በመቶ ዝቅ ማለቱን የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አስታወቁ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ መስከረም 28 ቀን 2005 የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ መክፈቻ ስብሰባ ላይ ያደረጉትን ንግግር አስመልክቶ ከምክር ቤት አባላት በቀረበው የማሻሻያ ሞሽን ላይ ተወያይቶ አጽድቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ከምክር ቤት አባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ ሲሰጡ እንደገለጹት የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር መንግሥት በገበያ ውስጥ ያለውን የገንዘብ መጠን በመቆጣጠር፣ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግና የንግድ ሥርዓቱን ዘመናዊ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት የዋጋ ግሽበቱ ዝቅ ብሏል። መንግሥት የሚያጋጥመውን የበጀት ጉድለት ለመሸፈን የብሔራዊ ባንክ ብድር ሳይወስድ የመንግሥት የግምጃ ቤት ሰነድን በመሸጥ የበጀት ጉድለቱ ከ1 ነጥብ 2 በመቶ እንዳያልፍ ማድረጉን አብራርተዋል። መንግሥት በጅምላ ንግድ ውስጥ የሚታዩትን ችግሮች ለማስወገድ ያካሄደው ጥናት በማጠናቀቁ የዋጋ ግሽበቱን ለመቆጣጠር ጥናቱ በዚህ ዓመት ተግባራዊ እንደሚደረግ ገልጸዋል። የዋጋ ግሽበቱን በመቆጣጠር ረገድ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ወሳኝ በመሆኑን በመገንዘብ ባለፈው ዓመት ከ1ሚሊዮን ኩንታል በላይ ማዳበሪያና ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ምርጥ ዘርፍ ለአርሶ አደሮች እንዲሰራጭ መደረጉን ተናግረዋል። የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት በተያዘው በጀት ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አቶ ኃይለማርያም አመልክተዋል። እንዲ