Posts

የኢሕአዴግ ታጋዮች ጡረታ ትግሉን ከተቀላቀሉበት ጊዜ ጀምሮ ሊሰላ ነው

Image
የቀድሞውን ወታደራዊ አገዛዝ የመገርሰስ ትግል ውስጥ የተሳተፉና በአሁኑ ወቅት በመንግሥት ተቋማት ውስጥ በማገልገል ላይ የሚገኙ የቀድሞ ታጋዮች ጡረታ (ማኅበራዊ ዋስትና) ትግሉን ከተቀላቀሉበት ጊዜ አንስቶ እንዲሰላ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ለሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት በጻፈው ደብዳቤ አሳሰበ፡፡ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ለመንግሥት ተቋማት የተሰራጨው ደብዳቤ ከሰኔ 13 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ እንደሆነና ይህም ማለት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሕይወት በነበሩበት ወቅት ነው፡፡  የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት ደብዳቤውን ያሰራጨው በሕግ ላይ ተመሥርቶ ይሁን አይሁን በእርግጠኝነት ለመናገር እንደማይችሉ የሪፖርተር ምንጮች የገለጹ ቢሆንም፣ ምናልባት ለሕዝብ ይፋ ያልሆነ መመርያ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ፀድቆ ሊሆን እንደሚችልና ደብዳቤውም በዚህ ላይ የተመሠረተ ሊሆን ይችላል ሲሉ ጥርጣሬያቸውን ገልጸዋል፡፡  ይህንን መረጃ በመንተራስ ሪፖርተር አንዳንድ በመንግሥት ሥራ ላይ የተሰማሩ የቀድሞ ታጋዮችን ለማነጋገር የሞከረ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) በአባልነት እያገለገሉ ያሉ ይገኙበታል፡፡ ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁት እነዚሁ የምክር ቤቱ አባላት የመረጃውን ትክክለኝነት ያረጋገጡ ሲሆን፣ የምክር ቤቱ ጽሕፈት ቤት ጉዳዩን አስመልክቶ ባቀረበው ጥሪ መሠረት ማንነታቸውን የሚገልጽ፣ ትግሉን የተቀላቀሉበትን ወቅትና በአሁኑ ጊዜ የሚያገለግሉበትን የመንግሥት ተቋምና ሌሎች ጉዳዮችን በተዘጋጀ ቅጽ ላይ መሙላታቸውን ገልጸዋል፡፡  ይህንን ቅጽ ከሞሉ በኋላ ደግሞ የምክር ቤቱ ጽሕፈት ቤት ከሰሞኑ በድጋሚ ማስታወቂያ እንዳወጣ፣ ማስታወቂያውም የተሞላውን ቅጽ ተንተርሶ የመንግሥት ሠራተኞች ማ

ክልሎች ከፌዴራል መንግሥት በሚጋሯቸው ገቢዎች ላይ ጥያቄ አነሱ

በዮሐንስ አንበርብር ክልሎች ከፌዴራል መንግሥት ጋር የሚጋሯቸው የተለያዩ የገቢ ዓይነቶች መከፋፈያ ቀመር ጊዜው ያለፈበትና አሁን ያለውን የዕድገት ደረጃ ያላገናዘበ በመሆኑ እንዲሻሻል ጥያቄ አቀረቡ፡፡ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ለፌዴራል መንግሥቱ ከሚሰጣቸው ሥልጣኖች አንዱ ከክልል መንግሥታት ጋር ያለውን የጋራ ገቢ እንዲሰበስብና ለክልሎቹ የሚገባቸውን ድርሻ እንዲያስተላልፍ ነው፡፡ በዚህም መሠረት የፌዴራል መንግሥትና የክልሎች የጋራ ገቢዎች የሚባሉት በሕግ ተወስነው ተለይተዋል፡፡ እነዚህም በፌዴራል መንግሥትና በክልሎች የጋራ ባለቤትነት ከተመሠረቱ የልማት ድርጅቶች የሚገኝ ገቢ፣ በክልል የተመሠረቱ ኃላፊነታቸው የተወሰነ የግል ማኅበራት (ፒኤልሲ) እና በክልሎች የሚገኙ የተለያዩ የተፈጥሮ ሀብቶችን ለማውጣትና ለመጠቀም ፈቃድ የተሰጣቸው ድርጅቶች ከሚከፍሉት ሮያሊቲ የሚገኝ ገቢ ናቸው፡፡ ከእነዚህ ዘርፎችና የገቢ ዓይነቶች የሚገኘውን ሀብት ክልሎች ከፌዴራል መንግሥት ጋር የሚከፋፈሉት በ1989 ዓ.ም በፌዴሬሽን ምክር ቤት ፀድቆ በሥራ ላይ እንዲውል በተደረገው ቀመር አማካይነት ነው፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በትናንትናው ዕለት ባደረገው ስብሰባ በዚህ ቀመር ላይ በዋነኝነት ተወያይቷል፡፡ የምክር ቤቱ የድጎማ፣ የበጀትና የገቢዎች ድልድል ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የክልሎችን ጥያቄ በመንተራስ፣ በዚህ ዓመት የገቢ ማከፋፈያ ቀመሩን ለመፈተሽ ዕቅድ ይዟል፡፡ የኮሚቴው ሰብሳቢ የሆኑት የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንቱ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት፣ ቀመሩ አሁንም በሥራ ላይ የሚገኝ ቢሆንም ቀመሩ ግን በቂ ግንዛቤ ያልተጨበጠበት እንደሆነ፣ ባለድርሻ አካላትና ክልሎች በቀመሩ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት እንዲሰጣቸውና እንዲሻሻል ተደጋጋሚ ጥሪ ማቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡ በአሁ

ደቡብ ግሎባል ባንክ በይፋ ሥራ ጀመረ

Image
አዲስ አበባ፡- በ266 ሚሊዮን 964 ሺ ብር የተፈረመና በ138 ሚሊዮን 901 ሺ 836 ብር የተከፈለ ካፒታል የተቋቋመው ደቡብ ግሎባል ባንክ በይፋ ተመርቆ ሥራ ጀመረ። ባንኩ በአዲስ አበባ በተለምዶ በቅሎ ቤት በሚባለው ስፍራ በሚገኘው ዋና መሥሪያ ቤቱ ትናንት ተመርቆ በተከፈተበት ወቅት የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ወርቁ ለማ እንደገለጹት፤ ባንኩ በ5ሺ 481 ባለ አክሲዮኖች የተቋቋመ ነው። ባንኩ የተከፈለ ካፒታል በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ ወደ አንድ ቢሊዮን ብር ለማሳደግ አቅዶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አመልክተው፤ ከነሐሴ 22 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ ለደንበኞቹ አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል። በባንክ ዘርፉ ያለው ውድድር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ ውድድሩን ለማሸነፍ ባንኮች አሰራሮችን ለማሻሻል የቅርንጫፉችን ቁጥር መጨመርና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ በአስፈላጊው ደረጃ ጥቅም ላይ ማዋላቸውን ገልፀዋል። እንደ ፕሬዚዳንቱ ገለፃ ባንኩ በወቅቱ ያለውን የውድድር ሁኔታ አሸናፊ ሆኖ በስኬት ጐዳና እንዲራመድ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት አቅዷል። ዘመናዊ የባንክ አሠራሮችን ተግባራዊ በማድረግ የወለድ አልባ ባንክ አገልግሎት የካርድና ኢ-ባንኪንግ አገልግሎቶች ለመስጠት ተዘጋጅቷል።  ባንኩ በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች ቅርንጫፎችን ለመክፈት መዘጋጀቱን ጠቁመው፤ በሚቀጥለው ሳምንት የሐዋሳና ሆሳዕና ቅርንጫፎች ሥራ እንደሚጀምሩ አመልክተዋል። የደቡብ ግሎባል ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ኑረዲን አውል በበኩላቸው በዕለቱ እንደገለጹት፤ ባንኩ በሥራ ላይ ባለው የመንግሥት ፖሊሲ ላይ በመመርኮዝ ለኢንቨስትመንትና በንግድ የሥራ ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶችን ጥረት ለመደገፍና ለባለአክሲዮኖች ተገቢውን ጥቅም ለ

ስለድጐማ በጀትና ገቢዎች ድልድል በቂ ግንዛቤ ለመፍጠር ታቅዷል

Image
አዲስ አበባ፡- በ2005 በጀት ዓመት የድጐማ በጀትና የገቢዎች ድልድልን በተመለከተ በቂ ግንዛቤ የማስፋፋት ሥራ እንደሚያከናውን ፌዴሬሽን ምክር ቤት አስታወቀ። በምክር ቤቱ የድጐማ በጀትና የገቢዎች ድልድል ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ትናንት በተካሄደው የምክር ቤቱ አራተኛ ዘመን ሦስተኛ ዓመት አንደኛ መደበኛ ጉባዔ ላይ የቋሚ ኮሚቴውን የ2005 በጀት ዓመት ዕቅድና የትኩረት አቅጣጫዎች ባመለከቱበት ወቅት እንደገለጹት፤ ዘንድሮ ግንዛቤ የማስፋፋት ሥራ ትኩረት ተሰጥቶት ተግባራዊ ይደረጋል። የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላትንና የቋሚ ኮሚቴ አባላትን አቅም መገንባት፣ የክልል መንግሥታት የገቢ አሰባሰብና የቀመር ባለሙያዎችን አቅም ማጠናከር እንዲሁም የክልል ምክር ቤት አባላት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትንና የልዩ ልዩ አደረጃጀቶች ተወካዮችን ግንዛቤ ማሳደግ ላይ በስፋት እንደሚሠራ ጠቁመዋል። የክልሎች ገቢ የመሰብሰብ አቅም የሌሎች አገሮችን ተሞክሮ በመውሰድና የአገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታ በመገምገም እንዲጠና የሚደረግ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሽፈራው፤ ሥራው በየወቅቱ መከናወን እንዲችልና ተቋማዊ ባለቤት እንዲኖረው ጥናታዊ አስተያየት ተዘጋጅቶ እንደሚቀርብ አመልክተዋል። ለድጐማ በጀት ቀመር ዝግጅት ከተለያዩ ምንጮች የተገኙ ልዩ ልዩ መረጃዎች ጥቅም ላይ የዋሉ ቢሆንም ለቀመር ዝግጅቱ ዋነኛ የመረጃ ምንጭ ሆኖ ያገለገለው ከደቡብ አፍሪካ ስታትስቲክሰ መሥሪያ ቤት የተገኘው እንደሆነ ገልጸዋል። በፌዴራል ደረጃ በአዲሱ የድጐማ በጀት ማከፋፈያ ቀመር ላይ አገራዊ መድረክ የማዘጋጀት ዕቅድ መኖሩን ያመለከቱት አቶ ሽፈራው፤ ከተያዘው የበጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ በተደረገው የድጐማ በጀት ማ

የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለማቃለል አገራዊ የህዝብ ንቅናቄ ይካሄዳል

Image
አዲስ አበባ፡-በየሥራ መስኩ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለማቃለል የሚያስችል ሕዝባዊና አገራዊ ንቅናቄ በተያዘው ዓመት እንደሚካሄድ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ አስታወቁ። የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ ትናንት የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የአራተኛ ዙር የሥራ ዘመን ሦስተኛ ዓመት የጋራ ስብሰባ በከፈቱበት ወቅት እንደተናገሩት፤ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለማስወገድና የተገኙ ስኬቶችን ለማስጠበቅ የሚያስችል አገራዊ እንቅስቃሴ በዚህ ዓመት ይካሄዳል። በአገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው መልካም አስተዳደርን የማጐልበት ሕዝባዊ ንቅናቄ የሚመለከታቸው አካላት የበኩላቸ ውን ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ አቅርበዋል። ሕዝባዊና አገራዊ ንቅናቄው በአሁኑ ወቅት በተጨባጭ የሚታዩ ችግሮችን ነቅሶ በማውጣት የመፍታትና የሕዝብን እርካታ የማረጋገጥ ግብ ያለው መሆኑን ፕሬዚዳንቱ አመልክተው፤ ለዚህ ግብ መሳካት ሁሉም ሕዝብ በንቃትና በተደጋጋፊነት እንዲሣተፍና የመልካም አስተዳደር ራዕዩን እውንነት እንዲረጋገጥ የዘርፉ ተዋናዮች ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ፕሬዚዳንቱ ገለፃ፤ ላለፉት 21 ዓመታት በሀገሪቱ ዴሞክራሲያዊና መልካም አስተዳደር የሰፈነበት ሥርዓት ለመገንባት በተደረገው ጥረት የዜጎችና የሕዝቦችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ለማስከበር ሰፊ እንቅስቃሴ ተደርጓል። ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን በፅናት ከማክበር ጀምሮ በነፃ የሕዝብ ምርጫ መንግሥትን እስከመመሥረት ድረስ በርካታ መሠረታዊ የዴሞክራሲያዊ ለውጥ ተግባራት ተከናውነዋል። ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን ለማስጠበቅና ለማጠናከር ሲባል የተቋቋሙት በየደረጃው ያሉት ምክር ቤቶች፣ የሕግ ተርጓሚና የአስፈፃሚው አካላት በሀገሪቱ የግልፅነትና የተጠያቂነት ሥር