Posts

በብአዴን እና በህወሃት ያገረሸው የውስጥ ሽኩቻ የሃይል አሰላለፍ

Image
በገዢው ሰፈር ጎራ ለይቶ ከተለኮሰው የቡድን ፖለቲካዊ ፍጥጫ እና ሴራ ጀርባ አገር እና ህዝብን የሚጎዳ አደገኛ ተግባር በግልጽ እና በስውርእየተካሄደ እንዳለ ከተለያዩ የፓርቲው ምንጮች የተገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ። በተለይ በብአዴን እና በህወሃት ቱባ አመራሮች መካከል ስር ሰዶ የቆየው እና የአቶ መለስን ህልፈት ተከትሎ ያገረሸው የውስጥ ሽኩቻ ሁለት ቡድኖች የሃይል አሰላለፋቸውን ለማጠናከር «ይረዱናል » የሚሏቸውን የሌሎች ፓርቲ ሹማምንት እና የመከላከያ የጦር አዛዦች ከጎን የማሰለፉን ተግባር ቀጥለውበታል።ለግንዛቤ እንዲረዳ የሃይል አሰላለፉን በጥቂቱ በመዳሰስ ወደ ዋናው ነጥብ እናምራ። ከበረከት እና ዓዜብ ጎን በመሰለፍ ቀዳሚ የሆኑት አቶ ተፈራ ዋልዋ እና አዲሱ ለገሰ ናቸው።አቶ አዲሱ በይፋ ከሚታወቀው የአየር መንገድ የቦርድ ሃላፊነታቸው ባሻገር ኮተቤ መስመር በሚገኘው እና «የአቢዮታዊ ዲሞክራሲ ማኔጅመንት ት/ቤት »ተብሎ በተከፈተው ተቋም ዋና ሃላፊ እና ለባለስልጣናት እንዲሁም ካድሬዎች መምህር ጭምር ናቸው። ከመለስ መታመም ወዲህ የህወሃት ካድሬ ላልሆኑ በአቶ አዲሱ እየተሰጠ ያለው ፖለቲካዊ ትምህርት ሳይሆን የበረከትን አቋም የሚያቀነቅን እና ህወሃትን የሚያጥላላ ቅስቀሳ ሆኖአል። በሌላ በኩል ዓዜብ ከጎኗ ማሰለፍ የቻለችው ጄነራል ሰአረ መኮንን እና እንዲሁም በእርሳቸው የሚመራውን ጦር ነው ።በተጨማሪም ቴዎድሮስ ሃጎስ ይገኛሉ ።የዓዜብ አስገራሚ “አቋም” በሶፊያን አህመድም ላይ ተንጸባርቋል።”ለኤርትራ ካሳ “በሚል 2.1 ቢሊዮን ብር ለሻብያ በሚስጥር እንዲሰጥ በፊርማቸው ጭምር ከወሰኑት መካከል አቶ መለስ ዜናዊ፣ሙሉጌታ አለም ሰገድ ፣ሟቹ አቃቤ ህግ መስፍን እና ሶፊያን አህመድ ይገኙበታል።ዓዜብ ከዚህ በመነሳት “መለስን የማይክዱ ታማኝ “ካለቻ

ጥቅት ስለ ይርጋዓለም ከተማ

Image
Irgalem  (also spelled  Yrgalam ,  Yrgalem  and  Yrga Alem ; alternate names include  Abosto ,  Dalle ) is a town in southern  Ethiopia . Located 260 kilometers south of  Addis Ababa  and 40 kilometers south of  Awasa  in the  Sidama Zone  of the  Southern Nations, Nationalities, and Peoples Region  (or  kilil ), the town has a latitude and longitude of 6°45′N   38°25′E  /  6.75°N 38.417°E  and an elevation of 1776 meters. It is the largest settlement in  Dale  woreda. Postal service is provided by a main branch; electricity and telephone service are also available. History Irgalem was occupied by the Italians 1 December 1936 during their campaign against the remaining Ethiopian Army of Sidamo under  Ras   Desta Damtew . The town was capital of  Sidamo Province  until after the 1975 takeover by the Derge regime, when it was moved to  Awassa . Around 1957 there was no telephone landline connecting Irgalem; telecommunications were provided by a radio station. The next ye

Postgraduate Scholarship Grant Announcement of IDRC Project

Image
Postgraduate Scholarship Grant Announcement of IDRC Project College of Agriculture at Hawassa University (HwU) announces full scholarship for 12 female and 8 research grants for female and male MSc students in  Human Nutrition, Soil Science and Plant Breeding  as part of the collaborative project entitled: " Improving Human Nutrition in Ethiopia through Plant Breeding and Soil Management " with University of Saskatchewan, Canada. The MSc research work will be carried out on farmers' fields and Professors from Hawassa University and University of Saskatchewan jointly supervise the students. The project is financed by International Research Center (IDRC) and Canadian International Development Agency (CIDA) through Canadian International Food Security Research Fund (CIFSRF). Deadline Date  - Until October 7, 2012 Hawassa University, School of Graduate Studies http://www.hu.edu.et/hu/index.php/85-hawassa-university/events/announcements/243-postgraduate-scholars

በመላ ሃገሪቱ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ተወካዩን መረጠ

Image
አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ በመላው ሀገሪቱ የተካሄደው የኢትዮጵያ ኡላማዎች የፈትዋና ዳዕዋ የወረዳና የቀበሌ ምክር ቤቶች ምርጫ በሰላም ተጠናቀቀ። በምርጫው በርካታ የእምነቱ ተከታዮች ከማለዳ  ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማና በተለያዩ የክልል ከተሞች በየምርጫ ጣቢያዎቹ በመገኘት፥ ይወክለናል ያሉትን እጩ ሀይማኖታዊ ስነ ሰርአቱ በሚያዘው መሰረት ሲመርጡ አርፍደዋል። በየምርጫ ጣቢያው 25 እጩዎች የተጠቆሙ ሲሆን ፥ ከመካከላቸው አብላጫ ድጋፍ ያገኙ 20ዎቹ የምክር ቤት አባላት ሆነዋል። አብላጫውን ድጋፍ ያገኙትና በከፍተኛ ድምጽ የተመረጡት አምስቱ የምክር ቤቱ ስራ አስፈጻሚ በመሆን፤ የስራ ድርሻቸውን እዚያው በህዝቡ መካከል የስራ ድልድል በማድረግ ቃለ መሃላ ፈጽመዋል። የእምነቱ ተከታዮችም በምርጫው ንቁ ተሳታፊ በመሆን ፥ ዕምነቱ የሚፈቅደውንና የአመራር ስርዓቱን  አጠናክረው ያስቀጥላሉ የሚሏቸውን እጩዎች ነጻ፣ ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊ እና አሳታፊ በሆነ መልኩ መርጠዋል። በምርጫው ወቅት የምርጫ ካርድ ያልወሰዱ መራጮች በመመዝገብ የመረጡ ሲሆን ፥ የመራጩ ቁጥርም ከተጠበቀው በላይ እንደነበር ነው የምርጫ አስፈጻሚዎቹ የጠቆሙት። በአዲስ አበባ የተለያዩ ክፍለ ከተሞችና በጅማ፣ በሃረር፣ በደሴ፣ በሻሸመኔ፣ በጎንደር እና በመቀሌ ሪፖርተሮቻችን በተዘዋወሩባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ፥  ያነጋገሯቸው ድምጽ ሰጭዎች አፍራሽ ሃይሎች ያደርጉት የነበረው ቅስቀሳና በምርጫው ወቅት ያዩት ነገር የተለያየና ፍጹም ሰላማዊ እንደነበር ነው የገለጹት። ተመራጮቹ የእስልምና ምክር ቤቶች አባላት የመረጣቸውን ህዝብ በቅንነት እና በታማኝነት እንዲያገለግሉ መራጮቹ የጠየቁ ሲሆን ፥ ተመራጮቹም የተጣለባቸውን ሃላፊነት ለመወጣት በአላህ

አንድነት ፓርቲ የፕሬስ አፈና እንዲቆም ጠየቀ

የፓርቲው ልሳን ጋዜጣ ወደ መጽሔት ሊቀየር ነው መንግስት በፕሬስ ላይ የሚያደርሰው አፈና እንዲቆም ያሳሰበው አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ፤ ከህትመት የታገዱት የፓርቲው ልሳን “ፍኖተ ነፃነት” እና “ፍትህ“ ጋዜጣ ለህትመት እንዲበቁ ጠየቀ፡፡ የፓርቲው አመራሮች ሰሞኑን በሰጡት መግለጫ፤ “ፍኖተ ነፃነት” ወደ ህትመት እንድትመለስና የፕሬስ አፈናው እንዲቆም ለጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ፣ ለመንግስት ኮሙኒኬሽን ሚኒስትር ለአቶ በረከት ስምኦን እንዲሁም ለብሮድካስት እና ለብርሃንና ሰላም ማኔጂንግ ቦርድ ደብዳቤ ቢጽፉም ምላሽ አላገኘንም ብለዋል፡፡ ልሳን ጋዜጣው ፓርቲው አባላቶቹንና ደጋፊዎቹን የሚያነቃበትና ከህዝቡ ጋር የሚገናኝበት ድልድይ እንደሆነ ጠቁሞ፤ መንግስት ይሄን ድልድይ ነው የናደው ብሏል፡፡ መንግስት ጋዜጣውን የዘጋው ሆን ብሎ ፓርቲውን ለማፍረስና በመጪው የአዲስ አበባ ማሟያ ምርጫ እንዳይሳተፍ ለማድረግ ነው ሲልም አክሏል፡፡ የጋዜጣውን መታገድና የፕሬስ አፈናን በመቃወም በቅርቡ ሠላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርጉ የገለፁት የፓርቲው አመራሮች፤ ህጋዊ ሠውነት ስላለን የሠላማዊ ሠልፍ ጥያቄያችን ተቀባይነት ያገኛል ብለን ተስፋ እናደርጋለን፤ ፈቃዱን ካላገኘን ግን የራሳችንን የትግል መንገድ እንከተላለን ብለዋል፡፡ አንድነት ፓርቲ የታገደውን ጋዜጣ ለመተካት ሁለት አፋጣኝ እርምጃዎችን ለመውሰድ መወሰኑን ገልፀው፤ አንዱ ጋዜጣዋን ወደ መጽሔት በመቀየርና ከግል ማተሚያ ቤቶች ጋር በመነጋገር በቀጣዩ ሳምንት ለገበያ ማቅረብ ሲሆን ሁለተኛው ፓርቲው የራሱን  የማተሚያ ማሽን በመግዛት ጋዜጦችን እራሱ ለማተም ውሳኔ ላይ መድረሱንም አመልክቷል፡፡ http://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&