Posts

ሲዳማን ማነው የወከለው?

ስሞኑን ከፌደራል እስከ ወረዳ ደረጃ የምገኙ የሲዳማ ኣመራር ኣባላት በሃዋሳ ከተማ በሲዳማ የወደፊት እጣ ፋንታ ላይ መክረው ባለ ዘጠኝ ነጥብ የኣቋም መግለጫ በማውጣት ኣጠናቀዋል። ኣንዳንዶች እንደምሉት ከሆነ የሲዳማ ኣመራሮች ዳግመኛ በሃዋሳ ከተማ ላለመሰባሰብ የወሰኑ ይመስላል፤ ምክንያቱም የሃዋሳን ከተማ ኣስተዳደር በሌሎች በሳል በምባሉ ብሄሮች እንድተዳደርላቸው ተሰማምተዋል እና ሃዋሳ ከእንግድህ የሲዳማ ኣስተዳደር ኣካል ባለመሆኑ በሃዋሳ ከተማ በሲዳማ ስም የመሰባሰብ እድል የላቸውም ይህንን እንኳን ኣርቆ ማየት ብሳናቸውም። ወደ ቁምነገሩ ስንመለስ የሲዳማ ህዝብ ኢህኣደግ ይጠቅመኛል በመልካምኣስተዳደር በኩል ያለብኝን ችግር ይፈታልኛል በማለት በተደጋጋሚ በችግሩ ጊዜ ፈጥኖ በመድረስ ሲመርጠው ብቆይም፤ ደኢህዴን / ኢህኣዴግ የሲዳማን ህዝብ ሲያሳዝን የሰሞኑ ክስተት የመጀመሪያው ኣይደለም። የዛሬ ኣስር ኣመት ደምኣፍሳሹ የደኢህዴን መንግስት የጸጥታ ኃይሎቹን ኣሰማርቶ በንጽሃን የሲዳማ ተወላጆችን ላይ በጠራራ ጸህይ የጥይት መዓት ኣውርዶ በርካታዎቹን በመግደል ሌሎቹን ኣቁስለዋል ፤ በድርግቱም የሲዳማ ህዝብ ክፉኛ ኣዝኗል፤ ሆኖም ከስህተቱ ይማራል ዳግመኛ መሰል ተግባር ኣይደግምም በማለት በባለፈው ምርጫ በነቅስ ወጥቶ እንደመረጠው ይታወሳል። ሰሞኑን ደግሞ ከባለፈው ስህተቱ ያልተማረው ደኢህዴን የሲዳማ ህዝብ ላሳየው ክብር እና ፍቅር የፓርቲው ኣመራሮች የሰጡት ምላሻ ራስን በራስ የማስተዳደር መብቱን በመንጠቅ የራሱን ከተማ በተቀጣሪዎች እንዲያስተዳድር ማድረግ ሆኗል። የምገርመው ደግሞ የሲዳማ የክልል ጥያቄን የሚያነሱ ኣካላት የሲዳማን ህዝብ የማወክሉ ናቸው ብለዋል። ለሲዳማ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ መብት መከበር ሲሉ በደኢህዴን እስር ቤቶች የሚማቅቁት ብሎም ተሰደው

አመራሮቹ በባለ ዘጠኝ ነጥብ በገለጹት የአቋም መግለጫቸው የሀዋሳን ከተማ የአመራር ስምሪት ከኪራይ ሰብሳቢነት የጸዳና ብቁ አመራር ከየትኛውም መዋቅር ቢመደብ ትግሉን ለማስቀጠል ቃል ገብተዋል፡፡

ባለፈው አመት ነሐሴ ወር ላይ ነበር በሀዋሳ ከተማ እና በሲዳማ ዞን በአንዳንድ ወረዳዎች ሁከት የመፍጠር አዝማሚያ የተከሰተው፡፡ የሲዳማ ህዝብ ጥያቄና ፍላጎት ነው በሚል የብሔሩን አቋምና ሀሳብ የማይወክሉ ግን ደግሞ ይህንኑ መንፈስ የያዙ ሁከት የመፍጠር አዝማሚያ መከሰቱ ይታወሳል፡፡ እናም የተፈጠረውን ሁኔታ ለመገምገምና ጉዳዩን ለማጣራት የብሔሩ ተወላጆች የሆኑ ከፌደራል እስከ ወረዳ ድረስ የሚገኙ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች የተገኙበት ግምገማ ለአንድ ሳምንት ተካሂዷል፡፡ በግምገማው ማጠቃለያ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ ሽፈራው ሹጉጤ እንዳሉት የተፈጠሩት ሁኔታዎች የኪራይ ሰብሳቢና የጸረ ሰላም ኃይሎች አጀንዳ እንጂ የሲዳማ ህዝብ ፍላጎት ያለመሆኑን ተናግረዋል፡፡ በወቅቱ የተፈጠረው ሁኔታ ለማርገብ የተደረገው ጥረት እንደተጠበቀ ሆኖ የኪራይ ሰብሳቢ እና የጸረ ሰላም ኃይሎች የህብረተሰቡን አቅጣጫ ለማስቀየር ያደረጉት ጥረት ያለመሳካቱንና ህልማቸው ቢሳካ ኖሮ በውስጠ ድርጅቱ ላይ የሚፈጥረው ተጽእኖ የከፋ ይሆን ነበር ብለዋል፡፡ የሲዳማ ህዝብ ከየትኛውም ብሔር እና ብሔረሰብ ጋር ተፋቅሮ እና ተከባብሮ የኖረ ወደፊትም የሚኖር ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳደሩ ይሁንና ኪራይ ሰብሳቢዎች እና የጸረ ሰላም ኃይሎች በወቅቱ የፈጠሩት አጀንዳ ይህንን ህብረ ብሄራዊነት ለማጥፋት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብ በታየባቸው አንዳንድ አመራሮች ላይም በየደረጃው በተካሄደው የሂስ ግለሂስ መድረኮች ላይ የእርምት እርምጃ መወሰዱንም የገለጹት ርዕሰ መስተዳደሩ በቀጣይም የኪራይ ሰብሳቢነትን አስተሳሰብ ከምንጩ የማድረቁ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ አመራሮቹ መንታ መንገድ የለም በሚል ርዕስ ለአንድ ሳምንት ያካሄዱትን ግምገማ ያጠናቀቁት በጋራ መግባባት

በገጠር የተደራጀ የጠና ልማት ሰራዊት ለመገንባት በተደረገው ጥረት የጤና አክስቴንሸን ፖኬጅ ሙሉ በሙሉ በመተግበር ስኬታማ ለውጥ እየታየ እንደሚገኝ በሲዳማ ዞን የሁላ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

Image
የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ታደሰ ካቢሶ እንደገለፁት በወረዳው ከ15ዐ  ሺህ በላይ አርሶ አደሮች 16ቱን የጤና ፓኬጆችን በግል፣ በቤተሰብ እንደዚሁም በህብረተሰብ ደረጃ ተግባራዊ በመደረጉ የተገኘው ውጤት አበረታች ነው፡፡ በአካባቢ ጤና አጠባበቅና በቤተስብ ጤና እንክብካቤ እንዲሁም ዋና ዋና ተላላፊ በሽታዎችን መከላከልና መቆጣጠር እንደተቻለም ኃላፊው ገልፀዋል፡፡ የሁላ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የሲቪል ሰርቪስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተረፈ ዳሞታ በበኩላቸው በወረዳው የተጀመረው የጤና ልማት ሠራዊት ግንባታ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱን እውን ለማድረግ የበኩሉን የሚወጣ ጤናማ ህብረተሰብ ለመፍጠር የሚያበረክተው አስተዋፅኦ የጎላ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ የዞኑ ጤና መምሪያ ተወካይ አቶ ቃሪሳ ዳፉርሳ እንዳሉት በዞኑ የጤና ኤክስቴንሽን ኘሮግራም ትግበራው ውጤት እየተመዘገበ በመሆኑ ቀጣይነት እንዲኖረው ክትትልና ድጋፍ ከባለሙያና አመራሩ ይጠበቃል ብለዋል ሲል የሲዳማ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ዘግቧል፡፡

ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት የተደነገገው ለፌስቡክ ብቻ ነው?

በሰለሞን ጥበቡ በዚህ ባለንበት በ21ኛው ክፍለ ዘመን ቴክኖሎጂ በፈጠረልን ምቹ ሁኔታ መረጃን በፍጥነትና በፈለግነው ቦታ መለዋወጥ አመቺ ሆኗል፡፡ ከእነዚህ መረጃን የመለዋወጫ መንገዶች ውስጥ ማኅበራዊ ድረ ገጾች ይገኙበታል፡፡ ፌስቡክ፣ ትዊተር፣ ታግድና የመሳሰሉት ከማኅበራዊ ድረ ገጾች የተወሰኑት ናቸው፡፡ እኔ በግሌ እነዚህ ከላይ የጠቀስኳቸው ማኅበራዊ ድረ ገጾች አካውንት ቢኖረኝም፣ በአንድ ወር አንድ ጊዜ እንኳን የማልከፍታቸውም አሉ፡፡ እንዲያውም ትዊተርን ከፍቼ አላውቅም ብል ይሻለኛል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ትዊተር ስለማልወድ አይደለም፡፡ ይልቁንም የትዊተር ተጠቃሚ ጓደኞች ስለሌሉኝና ምንም ዓይነት መረጃ ማግኘት ስላልቻልኩ ነው፡፡ ታዲያ ምንም ዓይነት መረጃ የማይገኝበትን አካውንት መክፈት በድንጋይ ላይ ውኀ እንደማፍሰስ ነውና ላለመክፈት ወሰንኩ፡፡ አሁን እንዲያውም ፓስወርዱ ጠፍቶብኛል፡፡ ስለዚህ ከትዊተር ጋር ፍቺ ፈጽሜያለሁ፡፡ ትኩስ መረጃዎች የማይገኙባቸው ሌሎች ድረ ገጾችም ዕጣ ፈንታቸው ይህ ነው፡፡ ከእኔ ጋር መፋታት፡፡ በኢትዮጵያ ብዙ ተጠቃሚ እንዳለው ወደሚነገርለት ፌስቡክ ስንመጣ ግን ከላይ ከጠቀስኳቸው ማኅበራዊ ድረ ገጾች በተቃራኒው ነው፡፡ ምክንያቱም ፌስቡክ ላይ ምን የሌለ ነገር አለና? ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ስፖርትና ሌሎችም ወቅታዊ ጉዳዮች እንደወረዱ የሚገኙበት ብቸኛው ቦታ ፌስቡክ አይደለም እንዴ? እውነቴን ነው የምላችሁ “መርካቶ ምን ጠፍቶ” የሚለው ማስታወቂያ ለሸቀጣ ሸቀጥ እንደሆነ ሁሉ፣ ትኩስ መረጃዎችን ለማግኘት ደግሞ ፌስቡክ ምን ጠፍቶ ማለት ይቻላል፡፡ የአገራችን ሚዲያዎች መረጃን ቶሎ አያደርሱም እየተባለ ይታማሉ፡፡ “ትዝብት ነው ትርፉ” ያለው ማን ነበር? መተዛዘብ ነው እንጂ ፌስቡክ ተጠቃሚ የሆነ እነርሱን ማን

የፖለቲካ ባህላችንን እንፈትሽ

በበላይ ዓለሙ ይህችን አጭር ጽሑፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝ ጳጉሜን 3 ቀን 2004 ዓ.ም. ማታ በአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ ጣቢያ የተላለፈው የአቶ ተስፋዬ ሐቢሶና የቅንጅት አባል የሆኑ ግለሰብ ውይይት ነው፡፡ ከጳጉሜን 3 ቀን በፊት ሁለት ግለሰቦች ያደረጉት ውይይት ካለ አልሰማሁምና አስተያየት መስጠት አልችልም፡፡ በዕለቱ በተደረገው ውይይት ሁለት ተፃራሪ ስሜቶች ናቸው የተሰሙኝ፡፡ አንደኛው መልካም ስሜት ሲሆን፣ ሌላኛው ግን ተቃዋሚዎቻችን እነዚህ ናቸው? እነዚህ ናቸው የአገራችን ተስፋዎች? የሚል የተስፋ መቁረጥ ስሜት ነው፡፡ በእርግጥ የቅንጅቱ አባል የተናገሩት የግል አቋማቸውን ይሁን የድርጅታቸውን መለየት ቢያስቸግርም፣ የሳቸውን የሚመስል ተመሳሳይ አቋም ከሌሎችም አንቱ ከተሰኙ ተቃዋሚዎች የሰማሁ ስለሆነ፣ የድርጅቱ አቋም ሊሆን ይችላል የሚል ኃይለኛ ጥርጣሬ ጭሮብኛል፡፡ የምሽቱ ውይይት ያተኮረው በቅርቡ በሞት የተለዩንን የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን አመራርን በተመለከተ ነበር፡፡ በእርግጥ አቶ መለስ ዜናዊን የሚያደንቋቸው ብዙ ኢትዮጵያውያንና የውጭ አገር ዜጎች እንዳሉ ሁሉ፣ በኃይለኛ የሚነቅፏቸውም በርካቶች ናቸው፡፡ በእነዚህ ሁለት ጽንፎች መሀል ያሉም አሉ፡፡ በምሽቱ በተደረገው ውይይት አቶ ተስፋዬ የኢሕአዴግ አባልና ደጋፊ ሳይሆኑ ስለ አቶ መለስ የሰጡት አስተያየት እጅግ አስደምሞኛል፡፡ በአንፃሩ የቅንጅት አባሉ የሰጡት አስተያየት እኚህ ሰው በእውነት የኢትዮጵያን ሁኔታ የተረዱ ሰው ናቸው ወይ? በእንደዚህ ዓይነት የተሳሳተ አመለካከት ነው ወይ አገርን መምራትና ሕዝብን ማሰለፍ የሚቻለው? አስብሎኛል፡፡ የጠራ የፖለቲካ መስመር ተጨባጩን አገር አቀፋዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታን በትክክል ከመገንዘብ ስለሚመነጭ፣ ምን ዓይነት መስመር ይሆን እነዚህ የተቃዋሚ ድርጅቶች የሚቀ