Posts

የሕግ ፍትህ እና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምን ሠራ?

Image
ባለፈው ዕትማችን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ ፍትህ እና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በ2004 ዓ.ም ያከናወናቸውን ተግባራት በተመለከተ ከኮሚቴው አባል የተከበሩ አቶ ዳዊት ተፈራ ጋር ባደረግነው ቃለ ምልልስ ማስነበባችን ይታወሳል፤ በዚህ እትማችን ደግሞ ቀሪውን ክፍል ይዘን ቀርበናል፡፡   ሕግ ከማውጣት አንፃር ቋሚ ኮሚቴው ያከናወናቸውን ተግባራት በተመለከተ አምስት ረቂቅ አዋጆችን ከሌሎች ቋሚ ኮሚቴዎች ጋር በመተባበር ሰርቷል፡፡ረቂቅ ሕጎቹ የሕግ አወጣጥ ሥርዓትን በተከተለ ሁኔታ ተረቅቀው የውሳኔ ሃሳብ ሪፖርት ቀርቦባቸው በምክር ቤቱ እንዲፀድቁ ተደርጓል፡፡ ሌላው ቋሚ ኮሚቴው ብቻውን የሚመለከተው እና ኃላፊነቱን ወስዶ በማርቀቅ ለምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳብ በማቅረብ የፀደቀው 'የወሳኝ ኩነት እና ብሔራዊ መታወቂያዎች' የሚለው አዋጅ ነው፡፡ በዚህ አዋጅ መሰረት የእያንዳንዱ ሰው ከልደት እስከ ሞት ያለው መረጃ ይመዘገባል፡፡ ለዚሁ ሥራ ከታች እስከ ላይ መዋቅር ያለው ጽ/ቤት ይቋቋማል፡፡ በአዋጁ መሰረትም እንደ ኢትዮጵያዊነት ለሁሉም ብሔራዊ መታወቂያ ይዘጋጃል፡፡መታወቂያው ሙሉ የማንነት መረጃን የያዘ ሲሆን ፤ለብሔራዊ ደህንነት እንዲሁም መንግሥት ሊዘረጋቸው ለሚፈልጋቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረተ ልማቶች ጭምር አጋዥ ነው የሚሆነው፡፡  ምንም እንኳን በበቂ ሁኔታ ተሳትፎበታል ለማለት ባያስደፍርም በረቂቅ አዋጁ ላይ ሕዝቡ ተሳትፎ እንዲያደርግበት ኮሚቴው ጥረት አድርጓል የሚሉት አቶ ዳዊት ረቂቁን ለማዳበር ከሚመለከታ ቸው አካላት ጋር የውይይት መድረክ ተፈጥሮ ጠቃሚ ግብአትም ከመገኘቱም በላይ ለጉዳዩ ቅርበት አላቸው ተብሎ ለሚታሰቡ ወገኖችና ተቋማትም ረቂቁ ላይ የበኩላቸውን ሃሳቦች ሰንዝረዋል። ሌላው ቋሚ ኮሚቴው ከሚያከናውናቸው

መረጃ:- የግልጽነትና የተጠያቂነት ቁልፍ መሳሪያ

ከኢፌዲሪ ህገ- መንግስት አምስት መሰረታዊ መርሆዎች ውስጥ የመንግስት አሰራርና ተጠያቂነት አንዱ ነው፡፡ የግልጽነትና የተጠያቂነት መርህ በመንግስት ሀላፊዎች የሚወሰዱ ውሳኔዎችና የስራ እቅስቃሴዎች ለህዝቡ ግልጽ መሆናቸውንና ህዝቡም ይህንን በተመለከተ ያሉትን መረጃዎች ለማግኘት ያለውን መብት የሚያረጋግጥ መርህ ነው፡፡ የግልጽነትና የተጠያቂነት መርህ የዲሞክራሲ ዋልታ በመሆኑም ከመርሁ ተግባራዊነት ውጪ ዲሞክራሲን ማስፈን የማይታሰብ ነው፡፡ ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት መጎልበት ትልቁን ድርሻ የሚይዘውን የህዝቦች ተሳትፎና የስልጣን ባለቤትነት ለማረጋገጥም ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት የመንግስት አሰራርን እውን ማድረግ የግድ ይላል፡፡ ዜጎች በፖለቲካና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግና የመንግስት ሀላፊዎች ሀላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ መሆኑን ለመመርመር ተገቢውን መረጃ ሊያገኙ ይገባል፡፡ ግልጽነትም ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ማድረግ ሲሆን ለተጠያቂነትም እንደ ቅድመ ሁኔታ ይቀመጣል፡፡ በመሆኑም የግልጽነትና የተጠያቂነት መርህ የህዝቦችን ተሳትፎ ከማሳደጉም በላይ የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብት የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ዜጎች መረጃ የመጠየቅ፣ የማግኘትና የማስተላለፍ መብታቸው መከበሩ አንድም ተሳትፎአቸውን ለማሳደግ ሌላም የግልጽነትና የተጠያቂነት መርህን በመተግበር የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ተግባራዊነትን ለማረጋገጥ የሚኖረው ድርሻ የጎላ ነው፡፡፡ ዜጎች መረጃ ለማግኘት በራሳቸው ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ በተጨማሪም ጠቃሚ የሆኑ መረጃዎችን በመፈለግና ለህዝቡ ተደራሽ በማድረግም የመገናኛ ብዙሀን ጉልህ ሚና አላቸው፡፡ የመገናኛ ብዙሀንና የመረጃ ነጻነት አዋጅ ቁጥር 590/2000 የመደንገጉ ምክንያትም የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብትንና የመገ

በቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባና ሌሎች የከተማዋ አስተዳደር ሃላፊዎች ላይ ፍርድ ቤት ትእዛዝ አስተላለፈ

Image
አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2005  (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የቀድሞውን የሀዋሳ ከንቲባ ጨምሮ በተለያዩ የሀላፊነት ቦታዎች ላይ በነበሩ የከተማዋ አስተዳደር ሃላፊዎች በተከሰሱበት በእነ አቶ እንድርያስ ኦሌሳ መዝገብ የተለያዩ ትአዛዞችን አስተላለፈ፡፡  ከመሬት ጋር በተያያዘ ያልተገባ ጥቅም ለራሳቸውና ለቤተሰቦቿቸው ለማስገኘት በማሰብ ስልጣንን ያለአግባብ በመጠቀም የተከሰሱት እነዚሁ የከተማዋ አስተዳደር የተለያዩ ሃላፊዎች የፍርድ ሂደት የሀዋሳ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲመለከተው ቢቆይም በነጻ አሰናብቷቸው ነበር፡፡ የከልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ጉዳዩን ማየት ከጀመረ በኋላ ግን ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ያልቻሉትን 1ኛ ተከሳሽ እንድሪስ አሎሳና 2ኛ ተከሳሽ ጉደታ ጎምቢ በፖሊስ ተፈልገው ሊገኙ ስላልቻሉ ስማቸውና ምስላቸው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ወጥቶ እንዲፈለጉ ትእዛዝ አስተላልፏል፡፡ ፍርድ ቤቱ በዚሁ መዝገብ የተከሰሱ የሌሎች 4 ተከሳሾች የዋስትና ጥያቄ ውድቅ በማድረግ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ትእዛዝ ማስተላለፉን ነብዩ ይርጋአለም ዘግቧል። http://www.fanabc.com/Story.aspx?ID=26121&K=

የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በ579 ሚልዮን ብር ግንባታ አጠናቀቀ

Image
አዋሳ መስከረም 18/2005 የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የቅበላ አቅሙን ለማሳደግ በ579 ሚልዮን ብር የጀመረው የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች ግንባታ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማዘጋጀቱን ገለጸ፡፡ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቱን ጨምሮ ሌሎች ተጨማሪ ፕሮጀክቶችን በ2 ቢልዮን 460 ሚልዮን ብር ወጪ እያካሄደ መሆኑን ገልጿል፡፡ የዩኒቨርስቲው የቢዝነስና ዲቨሎፕመንት ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ንጋቱ ረጋሳ ከትናንት በስቲያ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለፁት በዩነቨርስቲው ሜዲካልና ይርጋዓለም ካምፓሶች እንዲሁም በዋናው ግቢና ግብርናና ጤና ሳይንስ ኮሌጆች ከአንድ አመት በፊት የተጀመሩት አዳዲስ የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናቀዋል፡፡ ከተጠናቀቀው ፕሮጀክቶች መካከል በተለምዶ ኋይት ሀውስ የሚባለው የተማሪዎች ማደሪያ ፣ የመማሪያ ክፍሎች ቤተ መፃህፍት፣የአስተዳደርና የመምህራን ቢሮዎች ጨምሮ ሌሎችም ደረጃቸውን የጠበቁ ዘመናዊ መገልጋያዎች እንዳሏቸው ተናግረዋል፡፡ በሜዲካልና በይርጋለም ካምፓስ ብቻ በእያንዳንዳቸው 780 ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስማር የሚያስችሉ መሆናቸውን አመልከተው የፕሮጀክቶቹ ግንባታ በአሁኑ ወቅት ሙሉ ለሙሉ ተጠናቀው ተማሪዎች ተቀብሎ ለማስተናገድ እየተዘጋጁ ናቸው ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሰቲው በ460 ሚልዮን ብር ወጪ ባለፈው ዓመት ግንባታው ያስጀመረው የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አምስት ትላልቅ ዶርሚቴሪዎች በመያዝ እያንዳንዱ ዶርሚተሪ 780 ተማሪዎች ለማስተናገድ የሚያስችሉ ህንፃዎች ማካተቱን ተናግረዋል፡፡ በሁለት ሀገር በቀል ተቋራጮች የሚካሄደው የቴክኖሎጂ እንስቲትዩት 145 የመማሪያ ክፍሎች በተጨማሪ የአስተዳደር ቢሮዎች እና ሌሎችም ዲፓርትመንቶች ያካተተ ግዙፍ ህንፃ መሆኑን ከሁለት ዓመት በኋላ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ አስታውቀዋል፡፡ የቴክኖሎጂ እንስቲትዩቱ የሚ

ኮሚሽኑ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ሕጎችን በሦስት ቋንቋዎች በመተርጎም ያሳተመውን ሰነድ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስረከበ፤ በሲዳማ ኣፎ መቼ ነው መሰል ሰነዶች መቶርጎም የምጀምሩት?

Image
አዲስ አበባ መስከረም 15/2005 የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አገሪቱ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሕጎች፣ ስምምነቶችና መርሆዎችን በአማርኛ፣ በኦሮምኛና በትግርኛ ቋንቋዎች በመተርጎም ያሳተመውን ሰነድ ዛሬ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስረከበ። ኮሚሽኑ በሁለት ሚሊዮን ብር ወጪ ያሳተማቸውን 35 ሺህ "የሰብአዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች" ሰነድ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር አምባሳደር ጥሩነህ ዜና ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤትና ለኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶች አስረክበዋል። በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አዳራሽ በተካሄደው የርክክብ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አምባሳደር ጥሩነህ ዜና እንደገለጹት አገሪቱ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሕጎች፣ ስምምነቶችና መርሆዎች በሰብአዊ መብት ማስከበር ተግባር ላይ ሳይውሉ ቆይተዋል። እንዲሁም ወደ አገር ውስጥ ቋንቋዎች ለረጅም ጊዜያት ሳይተረጎሙ መቆየታቸውንም አስታውሰዋል። ኮሚሽኑ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ህጎቹን ወደተለያዩ ቋንቋዎች ተተርጉመው ዳኞች እና ዐቃቤ ሕጎች ከአገሪቱ ሕጎች ጋር አቀናጅተው እንዲጠቀሙባቸው ማሳተሙን አስረድተዋል። በአገሪቱ የሰብአዊ መብት ጥሰትን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ዳኞች እና ዐቃቤ ሕጎች "የሰብአዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች" ሰነድ በሥራ ላይ በማዋል ሊጠቀሙበት እንደሚገባም ገልጸዋል። እንዲሁም ለፌዴራልና ለክልል ሕግ አውጪ አካላት፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ በሰብአዊ መብት ዙሪያ ለሚሰሩ መንግሥታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች "የሰብአዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳኖች" ሰነዱን ለማሰራጨት የሚያስችል ስትራቴጂ የተነደፈ መሆኑን