Posts

Message to Newly Appointed Ethiopian Prime Minster

Image
From United Sidama Parties for Freedom and Justice (USPFJ), September 25, 2012 Ethiopia's newly-appointed Prime Minister Mr 'Hailemariam Desalegne' was sworn in on September 21ST 2012 in the Ethiopian capital Addis Ababa. Mixed opinions and reactions are pouring in from Ethiopians of all walks of life within the country and from the Diaspora. Numerous Ethiopians believe that, if the new PM takes the decision to be brave enough to think and act as a mature politician whose personal interest is put aside for the interest of the majority in the country, then there will be hope for all Ethiopians. He has before him the opportunity of establishing institutions that safeguard genuine democracy, freedom of expression and an independent system that accommodates and learns from divergent political opinions that will guarantee a respect for people's rights to hopes and opinions both individually and collectively, and which will guarantee that his name be well-remembered.

ቀይ መብራት --የሃይለማርያም ደሳለኝን እና የደመቀ መኮንን የተደበቀ ታሪክ

Image
አቶ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ደቡብ ክልል በነበሩበት ጊዜ የራሳቸውን የብሔረሰብ አካላት ወደ ስልጣን የመሰብሰብ ስራ ሲሰሩ ከሲዳማ ማህበረሰብ በኩል ለምን እኛስ ? የሚል ጥያቄ መነሳቱን የቅርብ ምንጮች ይጠቁማሉ ፤ አቶ ኃ/ማርያም ለዚሀ የሰጡት መልስ “ከእናንተ የተማረ ማህበረሰብ ስለሌለ ነው ካቢኔውን በተማረ ማህበረሰብ ያዋቀርኩት” የሚል መልስ ነበር (አንድ አድርገን መስከረም 10 2005 ዓ/ም)፡-  አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ የቀድሞ የውጭ ጉዳይ እና የቀድሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ፤ አቶ ደመቀ መኮንን የትምህርት ሚኒስትር ፤ አቶ ሶፊያን አህመድ የገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስትር ፤ እነዚህ  በስም የተዘረዘሩት ሶስት ከፍተኛ የሀገሪቱ ቱባ ባለስልጣናት የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ከዚህ ዓለም በህይወት በተለዩበት ወቅት የኢህአዴግ ፓርቲ ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ ለውድድር ያቀረባቸው ሰዎች ናቸው ፡፡ ፓርቲው ባደረገው ምርጫ መሰረት አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝን ሊቀመንበር ፤አቶ ደመቀ መኮንን ደግሞ የፓርቲው ምክትል ሊቀ መንበር አድርጎ መሾሙ የሚታወቅ ነው ፤ በቂ ድምጽ ያላገኙት በወ/ሮ አዜብ መስፍን የተጠቆሙት አቶ ሶፍያን አህመድ በሶስተኝነት ወደ ኃላ ቀርተዋል ፤ ነገ 11/01/2005 ዓ.ም ፓርላማው ምርጫውን በ99.6 በመቶ ድምጽ ያጸድቀዋል ተብሎ ይጠበቃል ፤  አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ የOnly Jesus እምነት ተከታይ ናቸው ፤ ምክትላቸው አቶ ደመቀ መኮንንና አቶ ሶፍያ አህመድ ደግሞ የእስልምና እምነት ተከታይ ናቸው ፤ በመሰረቱ ደመቀ መኮንን ብሎ የእስልምና እምነት ተከታይ ይኖራል ብለው ሰዎች ላያስቡ ይችላሉ ፤  አቶ ደመቀም ከወደ ወሎ መሆናቸው ሰዎች ይናገራሉ ፤ አሁን እኛን ያሳሰበን ነገር የኢህአዴግ የፓርቲ ምርጫ አይደለም ፤ የነዚህ ሰዎ

የፍጥጫው አካል የሆነው የመከላከያ ጄነራሎች ሹመት እንዴትና በማን ሹመቱ ተሰጠ? ጸደቀ?

የፍጥጫው አንዱ አካል የሆነው የመከላከያ ጄነራሎች ሹመት ይገኝበታል። በአንዳንድ ወገኖች የሚሰነዘር ተገቢ ጥያቄ አለ። «የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥና ጠ/ሚ/ር በሌለበት እንዴትና በማን ሹመቱ ተሰጠ? ጸደቀ?» የሚል ሲሆን፣ ለዚህ ደግሞ ከመንግስት አፈ ቀላጤዎች የሚስጠው ምላሽ ሹመቱ ቀደም ሲል በአቶ መለስ የጸደቀ እንደሆነ ሲናገሩ ተደምጠዋል። ይህ ግን ውሀ የማይቕጥር ነው ሲሉ የመከላከያ ምንጮች ማስተባበያውን ያጣጥላሉ። ምክንያቱንም ሲያስረዱ ከተሾሙት ጄነራሎች መካከል በአንጃነት ተፈርጀው የቆዩ፣ በመለስ በጥሩ አይን የማይታዩና ለረጅም አመት ለእስር የተዳረጉ እንዳሉም                              ይገልጻሉ። ሀቁ ይህ ሆኖ ሳለ መለስ እነዚህን  ይሾማሉ ብሎ ማሰብ ጨርሶ የማይታሰብ ነው ሲሉ ያክላሉ። እርከን ጠብቀው የተሾሙ  እንዳሉም ይጠቁማሉ። ቢሆንም ግን ህገ መንግስቱን ያልተከተለና ተገቢውን መንገድ  የልተከናወነ ሹመት እንደሆነ አልሽሽጉም። የብ/ጄኔራል ሹመት ከሰጣቸው አንዱ ኮ/ል አ ታክልቲ በርሄ  ይገኝበታል። ከዚህም ቀደም ባቀረብኩት መጣጥፌ «መለስ ካጠፋቸው የፓርቲው አባላት» ይኸው ኮ/ል እንደሚገኝበት ጠቅሼ ነበር። በተሰነይ ግንባር ከፍተኛ ጀግንነት የፈጸመው ኮ/ል አታክልቲ  ከጦርነቱ በሁዋላ መለስን ሀይለ-ቃል በመናገሩና በማውገዙ እስር ቤት ወርዶ ለረጅም አመት ድምጹ ጠፍቶ ቆይቶአል።በ 2000 አ.ም  ከእስር ተለቆ እንደቆየና በቅርቡ የብ/ጀነራልነት ሹመት አግኝቶ በተሻለ ሀላፊነት ላይ መቀመጡ ታውቆአል። ሌላዋ የሴት ጄነራል ተሿሚ አስካለ ብርሀኔ ትባ ላለች። ህወሀትን የተቀላቀለችው ከበርካታ ታዳጊ  እኩዮችዋ ጋር ሲሆን ጊዜው ደግሞ ግንቦት 1970 አ.ም ነበር። አብረዋት ጫካ ከገቡት ሴቶች ሁሉም ማለት ይቻላል

የኒዮሊበራሊዝም ቀውስና የአፍሪካ ተስፋ

አፍሪካ ምንም እንኳ ከሃምሳ ዓመታት በፊት ሙሉ ለሙሉ ከቅኝ ግዛት ብትላቀቅም መለያዋ ከሆነው ድህነት ነፃ መውጣት አልተቻላትም፡፡ «በአህጉሪቷ ድህነት ስር ሰዶ ሊነቀል በማይችል መልኩ ተተክሏል» የሚሉት በርካቶች ናቸው፡፡ ያደጉት አገሮችም አህጉሪቷ ከድህነት እንድትወጣ የሚያስችላትን አቅጣጫን ከማመላከት ይልቅ በየጊዜው ዕርዳታ እየሰጡ እጅ በመጠምዘዝ በፈለጉት መንገድ መምራቱን ነው የመረጡት። ያደጉት አፍሪካ አምርታ የምታገኘውን ውጤት ለዓለም ማቅረብ የማትችል እንደሆነች የበለፀጉት አገሮች ያስባሉ፡፡ አፍሪካውያን ለዘላለም ከድህነትና ከተረጂነት መላቀቅ እንደማይችሉ ይገምታሉ፡፡ እነርሱ ሊተገብሩት የሚፈልጉትን ነገር በአፍሪካ መሞከርም ምርጫቸው ነበር። አፍሪካ መሞከሪያ ከተደረገችበት ነገር ውስጥ አንዱ የኒዮሊበራሊዝም የኢኮኖሚ ርዕዮተ ዓለም አንደኛው ነው፡፡ በ1930ዎቹ መገባደጃ መወጠኑ የሚነገርለት ይህ ርዕዮተ ዓለም የሚያጠነጥነው ኢኮኖሚውና ገበያው ሙሉ ለሙሉ ከመንግሥት ውጪ ሆኖ ይንቀሳቀስ በሚለው መስመር ላይ ነው፡፡ በእዚህ አካሄድ ላለፉት ከሦስት ያላነሱ አስርት ዓመታት አፍካውያኑም ሆኑ ያደጉት ሀገራት ተግባራዊ ሲያደርጉት ቆይተዋል፡፡ ይህንን ርዕዮተ ዓለም ተግባራዊ ያደረጉ ሀገራት በተለይም የአፍሪካ ሀገራት ዕድገት ማምጣትም ሆነ ከድህነት መላቀቅ አልቻሉም፡፡ ያደጉት ሀገራትም ቢሆኑ ቀስ በቀስ ሊወጡት በማይችሉት የኢኮኖሚ ቀውስ ውስጥ ተዘፍቀዋል፡፡በተቃራኒው የኒዮሊበራ ሊዝምን ርዕዮተ ዓለም ከመቀበል የታቀቡ ሀገራት ደግሞ የራሳቸውን መንገድ ቀይሰው በመንቀሳቀሳቸው ከስህተታቸው እየተማሩ ፈጣን እድገት ማስመዝገብ ችለዋል፡፡  የ21ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያዎቹ አስርት ዓመታት ኒዮሊብራሊዝምን በሚከተሉና በማይከተሉ ሀገራት መካከል ግልፅ ልዩነት የታ

ቅድስት ማርያም ኮሌጅ ለአስራ ሶስተኛ ጊዜ በተከታታይ ርቀት ትምህርት ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ፤ እንኳን ደስ ኣላችሁ የሲዳማ ተመራቂዎች

Image
New አዲስ አበባ መስከረም12/2005 ቅድስተ ማርያም ኮሌጅ በዲግሪ ፣በዲፕሎማ እና በሰርተክፌት መርሀ ግብር ያስተማራቸውን 3 ሺ 325 ተከታታይ የርቀት ትምህርት ተማሪዎቹን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ እና በሀዋሳ ከተሞች አስመረቀ። ምሩቃኑ ትምህርታቸውን የተከታተሉት በቢዝነስ 1 ሺህ 498፣ በመምህራን ትምህርት ፕሮግራም 76፣ በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ፕሮግራም በደረጃ 4 መርሀ ግብር 1ሺህ 430 በደረጃ አራት ደግሞ 319 ተማሪዎች ናቸው ። ኮሌጅ ለአስራ ሶስተኛ ጊዜ በተከታታይ ርቀት ትምህርት ያስተማራቸውን ተማሪዎች ባስመረቀበት ፕሮግራሙ ላይ የኮሌጁ ፕሬዝዳንት ረዳት ፕሮፌሰር ወንደሰን ታምራት ባደረጉት ንግግር ምሩቃኑ የተማሩትን ትምህርት ወደ ተግባር በመለወጥ ለሀገራቸው ዕድገት የበኩላቸውን አስተዋፆኦ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል ። በክብር እንግድነት የተገኙት ታዋቂው የግብርና ሳይንስ ተመራማሪ ዶክተር ስሜ ደበላ ባስተላለፉት መልዕክት ተመራቂዎቹ ስራ ጠባቂ ሳይሆን ስራ ፈጣሪ በመሆን ራሳቸውንም ሌሎችንም ዜጎች መጥቀም እንደሚገባቸው ተናግረዋል ። በተለይ በቴክኔክና ሙያ ዘርፍ ተመራቂዎች በግብርና ዘርፍ ላይ ቴክኖሎጂዎችን በሰፋት በመጠቀም ኋላ ቀር የግብርና አሰራሮችን ለማስወገድ በሚደረገው ስራ ላይ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይኖርባቸዋል ሲሉ መናገራቸውን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል ።