ለመጪው መንግሥት አንኳር ምልከታ
በምሕረት ሞገስ ከጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሕልፈት በኋላ መጪው የኢትዮጵያ መንግሥት ማድረግ ከሚገባቸው ጉዳዮች ጥቂቶቹን የሚገልጹት በዓድዋ ሃሃይለ በሚባል አካባቢ የተወለዱትና ረዥሙን ዘመን በአሜሪካ አሳልፈው በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በልማቱ ዘርፍ የተሰማሩት አቶ ኃይለሚካኤል ገብረአናንያ ናቸው፡፡ አቶ ኃይለሚካኤል እንደሚሉት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ያረፉት ወሳኝ ወቅት ላይ ነው፡፡ ወሳኝ ወቅት ያሉበት ምክንያትም ከዚህ በፊት ያልታየ የልማት ብርሃን በኢሕአዴግ ዘመን በመታየቱ ነው፡፡ ከዚህ በፊት አፄ ቴዎድሮስ ሕይወታቸው ያለፈበት ምክንያት ኢትዮጵያን ለማሻሻል ያደረጉ በነበረው ተጋድሎ ነው፡፡ አፄ ምኒልክም ኢትዮጵያን ለማሻሻል ጀምረው፣ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴም ቀጥሎ ነበር፡፡ ተጨባጭ የሆኑና የሕዝብን ሕይወት የሚቀይሩ ልማቶች በተግባር የታዩት ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ዘመን ነው፡፡ አዲስ የጀመሯቸው ሥራዎች ደግሞ ከዚህ በፊት ከሠሯቸው በበለጠ የኢትዮጵያውያንን ሕይወት የሚቀይሩ ናቸው፡፡ የተጀመሩት አጀንዳዎች ተግባራዊ ሆነው ሳይጨርሷቸው መሞታቸው በወሳኝ ጊዜ ሞቱ ያስብላል፡፡ የሕዳሴው ግድብ ዋናው ነው፡፡ በእርግጥ በዓባይ ወንዝ ላይ ግድብ ለመሥራት በማቀድ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያ አይደሉም፡፡ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ ሰዎችን ስሜታዊ በሚያደርገው የዓባይ ግድብ ሥራን በመተግበር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ የባቡር መስመር ዝርጋታው፣ የስኳር ፕሮጀክቱ፤ በመሠረተ ልማቱም በሕክምናው፣ በግብርናው፣ በንግዱም፣ የመሳሰሉትም ለውጦች እየታዩ ነው፡፡ ጥራቱ አልተሻሻለም እንጂ ትምህርትም እየተስፋፋ ነው፡፡ ጥራቱን ማሻሻል ግን ግድ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲዎችና ትምህርት ቤቶች በየቦታው ስለተገነቡና መሠረተ ልማቱ ስለተ