የሀዋሳን ሀይቅ ከጥፋት ለመታደግ ድምፃችንን እናሰማ
ዛሬ መስከረም 1 ቀን 2005 ዓ / ም ሐዋሳ የፍቅር ሀይቅና አሞራ ገደልን የመጎብኘት ዕድል አጋጥሞናል፡፡ ባለፈው ዓመት ሚያዚያ 2004 ዓ / ም የሀዋሳ ሀይቅ ጠንቅ የሆኑ ችግሮች እንዲወገዱ አስተያየት ሰንዝሬ እንደነበር ይታወቃል፡፡ነገር ግን ዘንድሮም ይሄው ተመሳሰይ ችግር ምንም ለውጥ አልታየበትም ለአብነትም ያህል በቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኙ መዝናኛ ካፌዎች ዘመናዊ የሚመስል የቆሻሻ ማጠራቀሚያ /Dust Bin/ አስቀምጠዋል፡፡ለኔ የገረመኝ በፍቅር ሀይቅ በኩል በእግረኛ መንገድ አካባቢ ባለ አስር ሊትር ቢጫ የዘይት ጄሪካኖች ወገባቸው ተቆርጦ ለደረቅ ቆሻሻ ማጠራቀሚነት ተቀምጠዋል ይህ ሙከራ የማይጠላ ቢሆንም ፋይዳው ሲታሰብ ምንም የጠቀመው ነገር የለም፡፡ለምንድንው ግቢው የልማት ፅ / ቤት አለው ከተባለ ለምን ስርዓት ያለው የቆሻሻ መጣያዎችን በየቦታው ተቀምጠው አገልገሎት እንዲሰጡ የማያደርገው ? በአጠቃላይ እተሰራ ያለው ስራ ሀይቁን አመጥነውም፡፡ በየሀይቁ ዳር ሶስት እና አራት በጥቅም ላይ የዋሉ የውሀ መጠጫ ላስቲኮች፣ የሲጋራና የብስኩት መቅለያዎች፣የጫት ገራባና ጋዜጣዎች በየሀይቁ ዳር ተንሳፈው ታዝቤያለሁ፡፡ አስኪ አስቡት በቀን በትንሹ 20 የውሃ መጠጫ የያዙ ሰዎች የተጠቀሙበትን ላስቲክ በሀየቁ ዳር ቢጥሉ ከበርካታ ዓመታት በኋላ አላሙራ ተራራን የሚያክል ቆሻሻ ሊፈጠር ነው ማለት ነው፡፡ ፎቶ መላኩ ቀጥሎ ውደ አሞራ ገደል ጉዞ በእግር በማቋረጥ የተለመደውን አምስት ብር የደንቧን / የመግቢያ / ልከፍል ለምን ስራ እንደሚውል ስጠይቅ ለልማት ስራ ነው አሉኝ፣ለየትኛው ልማት ? ለአካባቢው ልማት አሉኝ አላለማችሁም ቆሻሻ እየተጣለ በትንሹ እንኳ ነገ ሀይቁ ከተበላሸ እናንተም ሰርታችሁ አትበሉም ሀዋሳም ያላት አይኗ ጠፋ ማለት ነው ስላቸው የሰለቻ