ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ መልካም እድል ለሲዳማ ተማሪዎች
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2 (ኤፍ ቢ ሲ)አገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ በ2005 የትምህርት ዘመን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገቡ ተማሪዎችን የመግቢያ ነጥብ ይፋ አደረገ፡፡ ሃገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ለፋና ብሮድካስቲነግ ኮርፖሬት እንዳስታወቀው በ2005 የትምህርት ዘመንበከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ተማሪዎች 116, 651 ሲሆኑ ፥ ከእነዚህም መካከል 75 ሺህ 69 (64.35%) ወንዶች እና 41,582 (35.64%) ያክሉ ደግሞ ሴቶች ናቸው። በተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት መስክ ለሁሉም መደበኛ ወንድ ተማሪዎች የመግቢያ ነጥብ 294 ሲሆን ፥ ለሴት ተማሪዎች ደግሞ 290 ሆኗል። ለታዳጊ ክልልና ለአርብቶ አደር ልጆች ወንድና ሴት ተማሪዎች 285 እና ከዚያ በላይ ሲሆን በተመሳሳይ ለግል ተፈታኞች ወንዶች 299 ለሴቶች 297 እና ከዚያ በላይ መሆኑን ገልጿል። በማኀበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስክ ሁሉም ለመደበኛ ተማሪ ወንዶች 275 ፥ ለሴት ተማሪዎች ደግሞ 270 እና ከዚያ በላይ ሲሆን ፥ በዚሁ የትምህርት መስክ ለታዳጊ ክልልና ለአርብቶ አደር ልጆች ወንድ ተማሪዎች 270 ለሴት ተማሪዎች ደግሞ 268 እና ከዚያ በላይ ሆኗል። መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች 270 እና ከዚያ በላይ እንዲሁም ለዓይነ ስውራን ተማሪዎች ደግሞ 230 እና ከዚያ በላይ እንደሆነም ኤጀንሲው አስታወቋል። እንዲሁም ለግል ተፈታኝ ወንድ ተማሪዎች 299 ለሴት ተማሪዎች ደግሞ 297 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ወደ ከፍተኛ ተቋማት እንዲገቡ መወሰኑን ገልጿል። በተመሳሳይም ወደ መሰናዶ የትምህርት መስክ የመግቢያ ነጥብ ለመደበኛና ለማታ ወንድ ተማሪዎች 2.57 ሲሆን ፥ ለሴት ተማሪዎች