Posts

Hawassa

Image
My flatmates, Mark and James, and I took a trip to Hawassa, the capital of Ethiopia’s Southern Nation, Nationalities, and People’s Region, this weekend. It was quite the experience but I haven’t yet had the opportunity to sort through the thoughts and emotions it conjured. James is a Finance Manager and wished to see some field projects. Hence, he was able to arrange a trip through Save the Children and he invited Mark and me along. We left Friday afternoon. The drive to Hawassa was nothing short of incredible; Beautiful fields with trees dotting the horizon, mountains towering in the distance, and lakes scattered across the land. A few things which I noticed, given my work with Save the Children, included that the herds were all tended by boys. The long distances the boys travel with their cattle leads many families to believe that boys are at greatest risk in times of food insecurity. However, boys have easy access to the products of the livestock, including milk. Girls are most

የመለስ ሕልፈት በኢሕአዴግ ጫንቃ ላይ የሚያሳርፈው ታላቅ ሸክም አለ

በክንፈ ኪሩቤል ተስፋሚካኤል የኢትዮጵያ ሕዝብ ጀግናዬ ነው የሚለው መሪውን መለስ ዜናዊን በሞት ካጣበት ቀን ጀምሮ አክብሮቱንና ፍቅሩን በታላቅ ሐዘንና እንባ ገልጿል፡፡ መለስ ላይመለስ አርፎአል፡፡ ዕድሜውን ሙሉ ዕረፍት ወስዶ አያውቅምና፡፡ ብዙዎች እንደ ተዝናኑት አልተዝናናም፡፡ እርግጥ ነው ሥጋዊ ደማዊ ለሆነ ሰብዓዊ ፍጡር ሁሉ ሞት አይቀሬ ነው፤ ምድራዊ ሥልጣን ዘለዓለማዊ አይደለም፡፡ ገንዘብ፣ ሀብትና ንብረትን ትቶ መሰናበት የግድ ነው፡፡ ነገር ግን ለአገር፣ ለወገንና ለሕዝብ ታላቅና አኩሪ ሥራ ሠርቶ ማለፍ ግን ክብር ነው! ሲዘከርም ይኖራል፡፡ ኢሕአዴግ ታላቅና ፈታኝ ሁኔታ ከፊቱ ተደቅኖበታል ሆኖም ግን ጥበብና ማስተዋል፣ ትዕግሥትና እርጋታ በተሞላበት እንዲሁም ጨዋነትና ይቅርባይነት በታከለበት መንገድ አመራሩን ከቀጠለ ሁሉንም መሰናክል ማለፍ ይቻለዋል፡፡ አቶ መለስ በትግሉና ከትግሉ በኋላ ራሳቸውን በኢኮኖሚክስና በማኔጅመንት ትምህርቶች አስተምረው ዕውቀትን ያገኙና ለአገራቸው ዕድገት የቀሰሙትን ዕውቀት ወደ ተግባርም የለወጡ ሰው ነበሩ፡፡ ስለ መለስ የአዕምሮ ችሎታ የሚወዷቸው ቀርቶ የሚጠሏቸው እንኳን አይክዱትም፡፡ ይህንን አይነት ሰው መተካት ለጊዜውም ቢሆን ይከብዳል፡፡ ስለ መለስ ባህርይ እንዲሁም ስለ ሥራዎቻቸው ጠንካራና ደካማ ጎን እንዲሁም ስለ ትክክለኛ ውሳኔያቸውና ስለ ስህተቶቻቸው የታሪክ ጸሐፊዎችና ተመራማሪዎች ወደ ፊት ይጽፉታል ብሎ የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ያምናል፡፡ ሆኖም ግን ለአንባብያን ማስታወስ የሚፈልገው ጉዳይ አለ፡፡ ይህ ጸሐፊ ከወራት በፊት በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ያሰፈረው ጽሑፉ በአጭሩ እንዲህ ይላል፡፡ ‹‹በተለይ አሁን እንደሚታየው ብዙዎቹ የአገሪቱ ቁልፍ መሪዎች በዕድሜ እየገፉ ናቸው፡፡ ብዙዎቹም በሥራ ድካምና በሕመም ያሉ ይኖራሉ፡፡ አን

በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ 283 የሚሆኑ ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጅ ለእረፈት የመጡ ወጣቶች የጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ ላይ ማሳተፋቸውን የወረዳው ወጣቶች ጽህፈት ቤት አስታወቀ::

በጽህፈት ቤቱ ወጣቶችን የማብቃት የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ መኮንን ዋይሶ እንደገለፁት ለበጎ ፍቃድ አገልግሎት የተሰማሩት  ወጣቶች በችግኝ ተከላ ፣ በጤና፣ በከተማ ፅዳት ፣ በማጠናከሪያ ትምህትና በተለያዩ ዘርፎች  ተሰማርተው ይገኛሉ፡፡ የወጣቶችን አቅም ለማጎልበት ጽህፈት ቤቱ  የድርሻውን እየተወጣ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ የማጠናከሪያ ትምህርት እየሰጡ ከሚገኙት መካከል ደምረው ደሹሬና ታመሩ ኤልያስ የእረፍት ጊዜያቸውን ሌሎችን በሚጠቅም ተግባር ላይ ማዋላቸው እንደሚያስደስታቸው ተናግረዋል፡፡ ትምህርቱን ከሚከታተሉት ተማሪዎች መካከል ያሬድ ገነሞ ከበጎ ፈቃደኞቹ እያገኘ ያለው ትምህርት ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ውጤታማ እንደሚያደርገው መናገሩን ቁምነገር ቦጋለ ዘግቧል፡፡

በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ የተማርነውን ለህዝብና ለሀገር መስዋዕትነት የሚያስከፍለውን ጠንካራ የሥራ መንፈስ በመከተል ከሚጠበቅብን የሥራ ግዴታ በላይ አስተዋፅኦ ለማድረግ ተዘጋጅተናል ሲሉ በሲዳማ ዞን ማልጋ ወረዳ ነዋሪዎች ገለፁ::

ነዋሪዎች እንዳሉት ድህነትን በልማት ለማሸነፍ የክቡር ጠቅላይ ሚኒሰተሩን ራዕይ በልባችን ይዘን በአዲስ የሥራ ባህል መታነፅ ጀምረናል ብለዋል፡፡ አንዳንድ አርሶ አደሮች በበኩላቸው ጠቅላይ ሚኒስተሩ የነደፉትን የግብርና ፖሊሲና ስትራቴጂን ተከትለው ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የድካማቸው ውጤት ከትውልድ ወደ ትውልድ ተሸጋግሮ ሲታወሱ እንዲኖሩ የበኩላቸውን ጥረት እንደሚያደርጉ ገልፀዋል፡፡ የተለያዩ የሀይማኖት ተቋማት አባቶችም በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት ምክንያት የደረሰብን ሀዘን የከፋ  ቢሆንም የተሰማን ቁጭት ዓላማቸውንና ራዕያቸውን ለማሳካት ብርታት ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡ የዞኑ የመንግስት ኮሚኒኬሽን እንደዘገበው፡፡ http://www.smm.gov.et/_Text/29NehTextN204.html

የኢህአዴግ ምክር ቤት በመስከረም ወር ሊቀ መንበሩን ይመርጣል

Image
አዲስ አበባ ነሃሴ 30/2004 የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲ ግንባር /ኢህአዴግ/ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ትናንት ማምሻውን ተጠናቀቀ። የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው የህዝቡን መነሳሳትና ለፓርቲው የሰጠውን አደራ ገምግሞ በታላቁ መሪ በሳል አመራርና በኢህአዴግ የተነደፈውን የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በከፍተኛ ርብርብ ለማሳካት ውሳኔ አሳልፏል። የህዝቡን ተነሳሽነትም የተለያዩ የህዝብ አደረጃጀቶችን በመደገፍ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየርና የተጀመረውን የህዳሴ ጉዞ በበለጠ ግለት ለማስቀጠልም ወስኗል። በገጠር በተፋሰስ ልማት፣ በመስኖና በተለያዩ የውኃ አሰባሰብ ዘዴዎች እንዲሁም በዘመናዊ የግብዓት አቅርቦትና የሙሉ ፓኬጅ አጠቃቀም ዙሪያ አርሶ አደሩን በማሳተፍና በመደገፍ የገጠር ልማት ሥራዎችን፣ የአርሶ አደሩን ምርታማነትና ተጠቃሚነት በከፍተኛ ፍጥነት ለማስቀጠል አጽንኦት ሰጥቶም መክሯል። በከተሞች የነዋሪውን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመረውን የጥቃቅንና አነስተኛ ልማትና የሥራ ዕድል ፈጠራ ለማስፋት በመረባረብ እንዲሁም በዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ ከፍተኛ ትኩረት የተሰጣቸውን የባቡር፣ የኢንዱስትሪዎችና የታላቁ ህዳሴ ግድብ ጨምሮ ሌሎች የኃይል ማመንጫ ተቋማት ግንባታዎችን ለማስቀጠል ሰፊ ምክክር አድርጓል። በተለይ መልካም አስተዳደርን ለማሻሻልና በራሱ ተሳትፎ የህዝቡን አደራ በብቃት ለመወጣት በሚቻልባቸው አቅጣጫዎች ዙሪያ አጽንኦት ሰጥቶ መክሯል። ኮሚቴው የመንግሥትን የገቢ አቅም የማጠናከር፣ ቁጠባና ኢንቨስትመንትን የማበረታታት፣ የዋጋ ግሽበትን የመቆጣጠር፣ የኤክስፖርት ገቢን የማሳደግ፣ ልማታዊ የግል ዘርፍን የማጎልበት ሥራዎችን አፈጻጸም በተመለከተ እስካሁን ያሉበትን ሁኔታዎች የቃኘ ሲሆን፣