Posts

የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ስምና ታሪክ ከመቃብር በላይ ሲታወስ እንዲኖር የሚደረጉ ተግባራትን እንደሚያከናውኑ በሲዳማ ዞን የዳራ ወረዳ ነዋሪዎች ገለፁ፡፡

Image
በተለያዩ የልማት ሥራዎች የተሰማሩ አንዳንድ የህብረተሰብ ክፍሎች በሰጡት አስተያየት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ህልፈተ ህይወት ምክንያት የደረሰብንን ቁጭት የምንወጣው የሳቸው ግብና ራዕይ ስናሳካ ነው ብለዋል፡፡ በምናስመዘግበው ውጤት ለዘላለም በሰማዕትነት እንዘክራቸዋለን ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ መጪው ትውልድ የእሳቸውን የሥራ ባህል እንዲወርስም ጥረት እንደሚያደርጉ መናገራቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ዘግቧል፡፡

የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ መልካም እድል ለሲዳማ ልጆች

New አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 28 (ኤፍ ቢ ሲ) የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የተማሪዎች ውጤት ይፋ ሆኗል። ከዛሬ ጀምሮ በኢንተርኔት ድረ ገጽ  www.nae.gov.et  መመልከት እንደሚችሉ የሀገር አቀፈ ፈተናዎች ኤጀንሲ ለፋና በሮድካስቲንግ ኮርፖሬት አስታውቋል። የተማሪዎች ውጤት በቀጣይ 10 ቀናት ውስጥ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የሚሰራጭ ሲሆን ፥ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም እና የመሰናዶ መግቢያ ውጤትም በቀጣይ ሁለት ቀናት ይፋ እንደሚሆን የሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ አርአያ ገብረእግዚአብሄር ተናግረዋል። በዘንድሮው አመት ፈተናውን የወሰዱ የመደበኛ ተማሪዎች ቁጥር 519,948 ሲሆኑ ከእነዚህም ውስጥ 283,712 ወንድ እና 236, 236 ሴቶች ናቸው። የዚህን ዓመት የ10ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤትን ስንመለከትም ፥ 67 ነጥብ 23 በመቶ የሚሆኑ መደበኛ ተማሪዎች ከ2 ነጥብ በላይ አስመዝግበዋል። ፈተናውን ከወሰዱ ተፈታኞች ውስጥ 1 ነጥብ 7 በመቶ የሚሆኑት 8 ሺህ 849 ተማሪዎች 4 ነጥብ ማምጣት የቻሉ ናቸው ተብሏል። ከእነዚህም ውስጥ 6 ሺህ 441 የሚሆኑት ወንዶች ሲሆኑ ሴቶች ደግሞ  የቀረውን 2 ሺህ 408 ቁጥር እንደሚይዙ ባህሩ ይድነቃቸው ዘግቧል። http://www.fanabc.com/Story.aspx?ID=25767&K=

የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢሕአዴግ/ ሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ ነገ ይሰበሰባል

Image
አዲስ አበባ ነሐሴ 28/2004 የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢሕአዴግ/ ሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ ነገ ማክሰኞ መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል፡፡ በነገው ዕለት በሚከፈተው የግንባሩ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አፈፃጸምን ይዳስሳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ኮሚቴው የ2004 በጀት ዓመት አፈፃጸሞችን በጥልቀት በመፈተሽ የግንባሩ ሊቀመንበር የነበሩትና የባለ ራዕዩና ታላቁ መሪ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ህልፈት ተከትሎ በሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብ የተስተጋባውን ቁጭትና እልህ በልማት ላይ በሚቻልበት ሁኔታ እንደሚነጋገር ለማወቅ ተችሏል፡፡ የታላቁን መሪውና በእሳቸው የተገነባውን የግንባሩና የአገሪቱ ልማታዊ መንግሥት ራዕይ ሁሉም በየተሰማራበት የስራ መስክ በመረባረብ ለማስቀጠል የገባውን ቃልና መነሳሳት የሚመጥን ዝግጅት ማድረግ በሚቻልባቸው ዙሪያም ኮሚቴው ይመክራል፡፡ በተጨማሪም ከኮሚቴው አባላት በሚነሱ አጀንዳዎች ዙሪያ በመምከር ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል ሲል ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል፡፡ http://www.ena.gov.et/story.aspx?ID=2329

Desecuritising quest for regional self-administration in Sidama-land

BY  Mulugeta Daye 8 hours ago  · (ከማህበራዊ መረብ ላይ የተገኘ ጽሁፍ) I am learning form the reports from the Sidama-land the reason Iyasu Ragaasa, Dukk’ale Lamiso, Boshla Gabiso, Abate Kimmo, et al jailed, they are alleged to mobilise people against government. If the allegations are correct, and even if those jailed people involved in mobilization of the Sidama-for regional self- administration. The commitment of late Prime-Minster Meles Zenawi to give constitutional guarantee to the Nations, Nationalities, and Peoples, to opt out from the Union which they are uncomfortable with as it is enshrined in article 39 of Ethiopian constitution, has become invalid while this visionary is in hospital bed. In the movement of 2005-2006 he legitimised the Sidama’s quest for regional autonomy. However he come down to the Sidama-land, capital and politely advised the nation to choose regional autonomy or development. For the Sidama both Regional autonomy and Development are the same thing. Because withou

ወ/ሮ አዜብ አቶ መለስን ለመተካት እየታገሉ ነው

Image
ነሀሴ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ወ/ሮ አዜብ መስፍን ባለቤታቸውን በሞት ካጡ በኃላ በእሳቸው እግር ተተክተው የህወሃትን የሊቀመንበርነት ቦታ ተቆናጥጦ ወደ ኢህአዴግ ምክትል ሊቀመንበርነት ለመሳብ ድጋፍ የማሰባሰብ ዘመቻ ላይ መክረማቸውን ምንጮቻችን ጠቆሙ፡፡ በኢህአዴግ 36 የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ውስጥ ብቸኛ ሴት ሆነው በመስከረም ወር 2003 ዓ.ም ከፍተኛውን የፓርቲ ሥልጣን በባለቤታቸው በአቶ መለስ ዜናዊ ልዩ ድጋፍ ማግኘት የቻሉት ወ/ሮ አዜብ የሰሞኑን ሐዘናቸውን ለድጋፍ ማሰባሰቢያ እንደተጠቀሙበት ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡ ወ/ሮ አዜብ ለድጋፍ ማሰባሰቢያ ይጠቅሙኛል የሚሉዋቸው የህወሃት ሰዎች ለቅሶ ለመድረስ ቤተመንግስት በሚመጡበት ወቅት አንገታቸውን እያነቁ በማልቀስና በማስለቀስ፣የማይፈልጉዋቸውን ደግሞ ፊት ሲነሱ መቆየታቸው በተለይ በአመራር ላይ ባሉት የብአዴን ሰዎች ዘንድ አልተወደደላቸውም፡፡ ወ/ሮ አዜብ ባለቤታቸው አቶ መለስ በ8ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ በጡረታ ያሰናበታቸው አቶ ሥዩም መስፍን፣አቶ አባይ ጸሐዬ፣አቶ አርከበ ዕቁባይ፣አቶ ተፈራ ዋልዋ፣አቶ አዲሱ ለገሰን “የመለስን ራዕይ ለማሳካት” በሚል ስትራቴጂ ከጎንዋ ለማሰለፍ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ መሰንበታቸውን ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡ ወ/ሮዋ በአቶ መለስ ቀብር ፕሮግራም ላይ በወ/ሮ ነጻነት አስፋው የተዘጋጀላቸውን ኦፊሻል ንግግር በመተው የራሳቸውን ኃሳብ ያንጸባረቁበት ንግግራቸው “መለስ የጀመራቸው ፖሊሲና ስትራቴጂዎች እስካልተበከሉና እስካልተበረዙ ድረስ …” የሚለው ንግግራቸው በመለስ ስም ለጀመሩት የድጋፍ ማሰባሰብ ጥረታቸው ይረዳቸው ዘንድ ሆን ብለው ያደረጉት መሆኑን ምንጫችን  አስቀምጦአል፡፡ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ከዚህ ሳምንት ጀምሮ ጉባኤያቸ