ወ/ሮ አዜብ አቶ መለስን ለመተካት እየታገሉ ነው
ነሀሴ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ወ/ሮ አዜብ መስፍን ባለቤታቸውን በሞት ካጡ በኃላ በእሳቸው እግር ተተክተው የህወሃትን የሊቀመንበርነት ቦታ ተቆናጥጦ ወደ ኢህአዴግ ምክትል ሊቀመንበርነት ለመሳብ ድጋፍ የማሰባሰብ ዘመቻ ላይ መክረማቸውን ምንጮቻችን ጠቆሙ፡፡ በኢህአዴግ 36 የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ውስጥ ብቸኛ ሴት ሆነው በመስከረም ወር 2003 ዓ.ም ከፍተኛውን የፓርቲ ሥልጣን በባለቤታቸው በአቶ መለስ ዜናዊ ልዩ ድጋፍ ማግኘት የቻሉት ወ/ሮ አዜብ የሰሞኑን ሐዘናቸውን ለድጋፍ ማሰባሰቢያ እንደተጠቀሙበት ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡ ወ/ሮ አዜብ ለድጋፍ ማሰባሰቢያ ይጠቅሙኛል የሚሉዋቸው የህወሃት ሰዎች ለቅሶ ለመድረስ ቤተመንግስት በሚመጡበት ወቅት አንገታቸውን እያነቁ በማልቀስና በማስለቀስ፣የማይፈልጉዋቸውን ደግሞ ፊት ሲነሱ መቆየታቸው በተለይ በአመራር ላይ ባሉት የብአዴን ሰዎች ዘንድ አልተወደደላቸውም፡፡ ወ/ሮ አዜብ ባለቤታቸው አቶ መለስ በ8ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ በጡረታ ያሰናበታቸው አቶ ሥዩም መስፍን፣አቶ አባይ ጸሐዬ፣አቶ አርከበ ዕቁባይ፣አቶ ተፈራ ዋልዋ፣አቶ አዲሱ ለገሰን “የመለስን ራዕይ ለማሳካት” በሚል ስትራቴጂ ከጎንዋ ለማሰለፍ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ መሰንበታቸውን ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡ ወ/ሮዋ በአቶ መለስ ቀብር ፕሮግራም ላይ በወ/ሮ ነጻነት አስፋው የተዘጋጀላቸውን ኦፊሻል ንግግር በመተው የራሳቸውን ኃሳብ ያንጸባረቁበት ንግግራቸው “መለስ የጀመራቸው ፖሊሲና ስትራቴጂዎች እስካልተበከሉና እስካልተበረዙ ድረስ …” የሚለው ንግግራቸው በመለስ ስም ለጀመሩት የድጋፍ ማሰባሰብ ጥረታቸው ይረዳቸው ዘንድ ሆን ብለው ያደረጉት መሆኑን ምንጫችን አስቀምጦአል፡፡ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ከዚህ ሳምንት ጀምሮ ጉባኤያቸ