በአንዳንድ የሲዳማ ወረዳዎች በርካታ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መታሠራቸውና ቀጥለው ባሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ እነሽፈራው ሊፈጽሙ ያሉት ክህደትና በህዝባችን በኩል መወሰድ ያለባቸው እርምጃዎች
የዚህ መልዕክት በጣም አጭር የሆነው ክፍል ከጉዳዩ አንገብጋቢነትና አጣዳፊነት አንጻር አስቀድሞ በጣም ባጠረ መልክ በ 2 ገጽ ተለቋል፡፡ ነገር ግን 2 ቱ ገጽ የተፈለገውን መልዕክት አሟልቶ ማስተላለፍ ስለማይችል ይህ ጽሁፍ እንዲዳረስ ለማድረግ ተወስኗል፡፡ የተከበራችሁ አባቶቻችን ( ሽማግሌዎች ) ፣ የተወደዳችሁ ተማሪዎች፣ የተከበራችሁ ነጋዴዎችና አርሶአደሮች፣ ውድ ምሁራን አሁን ያለንበት ወቅት ከምን ጊዜውም በላይ ፈታኝ መሆኑ የማይታበል ሀቅ ነው፡፡ ያለነው ከምን ጊዜውም በላይ መብታችን ተረግጦ፣ ህገ - መንግሥታዊ ጥያቄያችንንና ክልል ለመሆን ያስተላለፍነው ውሳኔያችንን ተከልክለን ባለንበት ሁኔታ ነው፡፡ የህዝብ ቁጣ ተባብሶ ባለበት ሁኔታ አሁንም የባሰ ክህደት ሊፈጽሙ እየሠሩ መሆኑ ስለተደረሰበት ይሄንን መልዕክት ማስተላለፍ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በቀጣይ ጥቂት ቀናት ውስጥ እነሽፈራው ከየወረዳው ሁሉም ቀበሌዎች ቢቻል የራሱ ዘመድ የሆኑና ታማኝ የሆኑ ሽማግሌዎችን ካልተቻለም የዋህ የሆኑና ለማታለል የሚመቹ ሰዎችን ወደ ሐዋሳ ጠርተዋል፡፡ ዋና የማደናገሪያ አጀንዳቸው፡ - የህዝብ ጥያቄው ተመልሷል፡፡ በከተማው በሁሉም የሹመት ቦታዎች የሲዳማ ተወላጆች ተሹመውበታል፡፡ የክልል ጥያቄ ለማንሳት ግን አሁን ጊዜው አይደለም አይጠቅመንም፡፡ ስለዚህ ተውት የሚል ነው ፡፡ እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት ይሄንን ሴራ የጠነሰሱት ከሁሉም ቀበሌያት ያን ሁሉ አመራርና የተገኘ ሽማግሌ ሁሉ ጠርተው ሲዳማን የሚወክል ሰፊ ህዝብ የተስማማ ለማስመሰል የተለያዩ የዜና አውታሮችን ( የመገናኛ ብዙሃንን ) ጠርተው የተለመደውን ውሸታቸውን ሊያስተጋቡ ተዘጋጅተው ነው፡፡ እዚህ ጋ ልብ ልንል የሚገባው ተሰብሳቢዎች የተናገሩት ሳይሆን የሚተላለፈው በዋናነት የውሸትና