Posts

የሲዳማ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ በዓል ተከበረ

ሀዋሳ ነሃሴ 9፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) በየዓመቱ የሚከበረው የሲዳማ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ በዓል /ፍቼ ጫምባላላ/ ትናንት በሀዋሳ ከተማ ተከብሯል። በሲዳማ ባህል አዳራሽ በተካሄደው ክብረ በዓል ላይ በተለያዩ ምሁራን የተዘጋጁ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ የሲዳማ ብሔረሰብ  ቋንቋው ፣ ባህሉና ማንነቱ ተክብሮለት ከሌሎች የሀገሪቱ ብሔር ብሔርሰቦች ጋር ተቀናጅቶ ለአገሪቱ ብልፅግና እየሰራ መሆኑን የደቡብ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ በስነ ስርዓቱ ላይ ተናግረዋል ፡፡ የዘመን መለወጫ /ፍቼ  ጫምባላላ/ ባህላዊ የአከባበር ስነ ስርዓት በመንግስታቱ ድርጅት የሳይንስ ፣ የትምህርትና ባህል ድርጅት/ ዩኔስኮ / በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ ጥረት በመደረግ ላይ መሆኑም ተመልክቷል፡፡ ከዘመን መለወጫው በዓል ጋር ተያይዞ የብሔረሰቡ 18ኛው የቋንቋና ባህል ስምፖዚየም መካሄዱን ነው ኢዜአ የዘገበው፡፡

የፊቼ በዓል በኣለም በሰው ልጅ ቅርስነት እንዲመዘገብ የሲዳማ ቋንቋ ሲምፖዚዬም ተሳታፊዎች ጠየቁ

Image
በዛሬው እለት በሃዋሳ ከተማ የሲዳማ ባህል ኣዳራሽ የተከሄደው የሲዳማ ቋንቋ ስምፖዚዬም  በተለዩ ቋንቋውን ለማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት ኣካሄደ፤ በውይይቱ ላይ ከእስራኤል ሂብሩ ዩኒቨርስቲ የመጡት ዶክተር ኣንበሴ እና የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሰፍ ማሞን  ጨምሮ  በርካታ የሲዳማ ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል የ ቀኑን ውሎ በተመለከተ የሚከተለውን ሪፖርት ያንቡ፦ Today the Sidama Nation Successfully defended its rights during the Sidama Language symposium that took place in Sidama Capital- Hawassa, in Sidama cultural Hall. On today's (14 August 2012) Symposium three major decisions were made by the Sidamas independent Scholars involving Dr Anbese from Israel's Hebrew University and Dr Yosef Mamo, Dean at Hawassa University among others prominent Sidama intellectuals. The deliberation of the Sidama Scholars and the entire Sidama participants include:- The Sidama language is not given appropriate attention to develop to date, it must be given the respect it deserves based on suggestions of Sidama's international renown aforementioned linguist. The language also must be one of the

የሲዳማን ኣዲስ ኣመት የፊቼን በኣል በደማቅ ሁኔታ ለማክበር ዝግጅት በመጠናቀቅ ላይ ነው፤ የሲዳማ ቋንቋ ስምፖዚዬም እና ጫምባባላ በነገው እለት በሲዳማ ባህል ኣዳራሽ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራሉ፤ ከፊቼ በኣል ጋር በተያያዘ በሃዋሳ ከተማ የጸጥታ ቁጥጥሩ መጥበቁ እየተነገረ ነው

በሃዋሳ ከተማ ነገ እና ከነገ ወዲያ የሚከበሩት የጫምባባላ እና የፊቼ በኣል፤ የሲዳማ ህዝብ መለያ እሴቶች በመሆናቸው ልዩ ትኩረት ስጥተው ለማክበር የተለያዩ ዝግጅቶት ተደርገው በመጠናቀቅ ላይ መሆኑ ተገልጿል። በበኣሉ ላይ ከሁሉም የሲዳማ ወረዳዎች የታጋበዙ ሰዎች ተሳታፊ እንደምሆኑ ሲገለጽ፤ በነገው እለት የጫምባባላ በኣል በሲዳማ  ባህል ኣዳራሽ ከሲዳማ ቋንቋ ስምፖዚዬም ጋር በጥምር ይከበራል። የዞኑ ማስታዎቂያ እና ባህል መምሪያ የቋንቋ ስምፖዚዬሙን ኣስመልክቶ ያዘጋጃቸውን ቲሸርት እና ኮፊያ ለበኣሉ ተሳታፊዎች በማደል ላይ ሲሆን፤በዚምፖዚዬሙ ላይ የሲዳማን ቋንቋ እና ባህል በተመለከተ ጥናታዊ ጽሁፎች እና ውይይቶች ይካሄዳሉ ተብሎ ይጠበቃል። በሲዳማ ባህል ኣዳራሽ ዝግጅት ላይ እንድገኙ የተለያዩ የመንግስት ባላስልጣናትን ጨምሮ  ታዋቅ ሰዎች እና የሃዋሳ ከተማ  ነዋሪዎች ተጋብዘዋል። የፊቼ በኣል ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ ከሲዳማ ህዝብ ወጪ በዞኑ ነዋሪ በሆኑ በሌሎች ብሄሮችም ጭምር እየተከበረ ያለ ሲሆን፤ ከሌሎች ኣካባቢዎችም  በርካታ ሰዎች በኣሉን ከሲዳማ  ህዝብ ጋር ለማክበረ ወደ ሃዋሳ ከተማ ይመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። የሃዋሳ ከተማ  ኣስተዳዳር እና የሲዳማ ዞን ለበኣሉ ድምቀት የፖሊስ ማርሽ ኦርኬስትራ ያስመጡ ሲሆን፤ የፖሊስ ኦርኬስትራው  የተለያዩ ጣእመ  ዜማዎችችን  በበኣሉ ያቀርባል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ካለፈው ወር ጀምሮ ከሲዳማ ክልል ጥያቄ ጋር በተያያዘ በሲዳማ ዞን ውስጥ ተነስቶ የነበረው  ህዝባዊ  ንቅናቄ  በፊቼ  ኣከባበር ላይ ችግር ልፈጥር ይችላል በምል የጸጥታ ቁጥጥሩ መጥበቁ እየተነገረ ሲሆን፤ ከሃዋሳ መግቢያ ላይ በተለይ ሞኖ ፖል ላይ ግለሰቦች የጦር መሳሪያ ይዘው ወደ ከተማ እንዳይገቡ እየተፈሹ ነው።

ኣንዳንድ በሲዳምኛ ቋንቋ ላይ የተሰሩ ጥናቶች

STUDENTS' ATTITUDE TOWARDS MOTHER TONGUEINSTRUCTION AS A CORRELATE OF ACADEMIC ACHIEVEMENT: THE CASE OF SIDAMA ABSTRACT The purpose of this study is to investigate students' attitude towards Sidamalanguage as a medium of instruction and its determination on the languageachievement.To carry out this aim, 391 students' were chosen from 7 Sidama Zone upperprimary schools. In addition to background information students were given withattitude and motivation questionnaires to measure their inclination towards the nativelanguage instruction. In the mean time students' one year cumulative GPA of Sidamalanguage were obtained from the record offices.Stepwise multiple regression analysis was conducted to find out the combinedand independent effect of the independent variables. Path analysis was employed toexamine the relationships among the predictor variables and between the predictorvariables and the criterion variable. Comparison of means and chi-square technique

የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ በሲዳምኛ ቋንቋ በመጀመሪያ ድግሪ የትምህርት ፕሮግራም ሊከፍት ነው፡፡

Image
ሃዋሳ ነሃሴ 6/2004/በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የብሄር ብሄረሰቦችን ቋንቋ ለትምህርትና ለምርምር ስራ ለማዋል እየሰራ መሆኑን የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት አስታወቁ፡፡ የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ የሲዳምኛን ቋንቋን ለመጀመሪያ ጊዜ በድግሪ የትምህርት ፕሮግራም ለመጀመር መዘጋጀቱም ተመልክቷል፡፡ የሲዳምኛን ቋንቋን በመጀመሪያ ድግሪ ደረጃ ለማስተማር የተቀረጸው የስርዓተ ትምህርት ለመገምገምና የማዳበሪያ ሀሰብ ለማከል ትናንት በሀዋሳ ከተማ የምክከር መድረክ ተካሂዷል ። የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ በምክክር መድረኩ ላይ እንደገለጹት የሀገራችን ብሄር ብሄረሰቦችን ማንነትን፣ ባህል፣ ታሪክና ወግ የሚጠናበትና የሚታወቅበት መንገድ ለማመቻቸት ራሱን የቻለ የቋንቋ ጥናት ትምህርት አስፈላጊ ነዉ ። ዩኒቨርስቲው በደቡብ ክልል ከ54 በላይ ብሄር ብሄረሰቦች ማዕከል በሆነችው ሀዋሳ ከተማ እንደመገኘቱ አሁን በሲዳምኛ ቋንቋ በድግሪ ደረጃ የትምህርት ፕሮግራሙን ለመክፈት የተደረገዉ ዝግጅት ተጠናቆ ከያዝነው ክረምት ጀምሮ ወደ ተግባርይሸጋግራል ብለዋል ። በሲዳምኛ ቋንቋ በድግሪ ደረጃ የሚጀምረዉ የትምህርት ፕሮግራም በማስፋፈት ወደፊት የሌሎችንም ብሄር ብሄረሰቦችን ቋንቋ በተመሳሳይ የመማሪያና የምርምር ስራ ለማዋል እቅድ መኖሩንም ዶክተር ዮሴፍ አስታውቀዋል፡፡ በተለያዩ ቋንቋዎች የመጀመሪያ ድግሪ ፕሮግራም መከፈት የብሄር ብሄረሰቦችን ባህላዊ እሴት ከማሳደግ ባለፈ ሌሎች ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ተናግረዋል ፡፡ የዩኒቨርስቲው የሶሻል ሳይንስና ሂዩማኒቲ ኮሌጅ ዲን ዶክተር ንጉሴ መሸሻ በበኩላቸው የሲዳምኛን ቋንቋን በድግሪ ፕሮግራም በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያ መሆኑን ገልጠዋል ። በዚህ የትምህርት ደረጃ መኖሩ የብሄርሰቦች አፍ መፍቻ ቋ