Posts

በደቡብ ክልል በፕሬዚዳንቱና በአፈ ጉባኤዋ መካከል በተፈጠረው ውዝግብ ምክር ቤቱ ለሁለት ተከፈለ

ሐምሌ ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ባለፈው ማክሰኞ የክልሉ ፕሬዚዳንት የሆኑት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ከሲዳማ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ የአገር ሽማግሌዎችን ሰብስበው “የሲዳማ ጥያቄ ፣ ወቅታዊ አለመሆኑንና አብዛኛውን ህዝብ የማይወክል መሆኑን” ተናገሩ በማለት ለማግባባት ሞክረው እንደከሸፈባቸው መዘገባችን ይታወሳል። ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ከሌሎች የመገናኛ ብዙሀን የተወከሉ ጋዜጠኞች በስፍራው ተገኝተው “የሲዳማ ጥያቄ  የጸረ ሰላም ሀይሎች ጥያቄ ነው” በማለት ይዘግባሉ ተብሎ ሲጠበቅ፣ ስብሰባው በውዝግብ ተደምድሟል። ይህን ተከትሎ ፕሬዚዳንቱ የዞኑን እና የወረዳዎችን ከፍተኛ ባለስልጣናት ትናንት ሰብስበው፣ ህዝቡን የማሳመን ስራ በበቂ ሁኔታ ባመለስራታችሁ ተጠያቂዎች ናቸው ብለው ሲናገሩ፣ የዞኑ አፈ ጉባኤ የሆኑት ሴት ” የህዝቡ ጥያቄ በህገመንግስት የተቀመጠ ጥያቄ ነው ይህንን በህገመንግስት የተቀመጠ መብት፣ አይገባህም ብለን ልናሳምን አቅሙም የለንም፣ አንችልምም፣ ይህ ጥያቄ እኮ የኔም ጥያቄ ነው።” በማለት መልሰዋል። የአፈ ጉባኤዋን መልስ ተከትሎ አብዛኛው የምክር ቤት አባላት ” እኛ ጥያቄው የህዝብ ነው፣ ከህዝብ ጋር የምንጣላበት ነገር አይኖርም ፣ ህዝቡን መብታችሁን አታስከብሩ በማለት አንቀሰቅም” በማለት በሀይለቃል መናገር በመጀመራቸው ስብሰባው ያለውጤት እንዲበተን ተደርጓል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰሞኑን በዞኑ በርካታ ተነሱ የሚል ይዘት ያላቸው ወረቀቶች በብዛት እየተሰራጩ ነው። የዞኑ ባለስልጣናት እርስ በርስ መከፋፋላቸውን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተለው ዘጋቢያችን ገልጧል።

የሃዋሳ ሀይቅ ቲላፒያ እና ካትፊሽ

Image
Fishing boats on the side of Lake Hawassa, Awassa in the Rift Valley of Ethiopia. Opening with a view of lake from a park next to the shoreline where fish is allowed to be landed, we move to the beach where about twenty 20' wooden rowing boats were landing their catch. People were taking the fish caught in the nets into the boat, the nets were carefully folded back onto the back of the boats, and the boatmen were selling the fish (a very fast transaction). Fish gutting took place while standing in the water (with the storks enjoying the guts), then taking the fish to a hall above the beach where they were filleted and the fillets skinned. Some fish were taken straight to the shops and deep-fried over wood fires for immediate consumption. Only two species appeared to be caught: tilapia in large numbers, and a few catfish. The size of the catch seems to be restricted firstly by the size of the nets, and all the tilapia appeared to be very similar in size, sugges

የሃዋሳ ኣሞራ ገደል የኣሳ ገበያ

Image
Lake Awassa lies to the west of Awassa town, approx. 275 km south of Addis Abeba, the capital of Ethiopia. The lake supplies Awassa with all its water, and supports a thriving local fishery. Many earn their living either through fishing or related tea and food businesses along the shore. More and more fishermen, though, nets with too small mesh, where already small fish gets caught, fish and other waste thrown back into the lake and soil erosion are leading to an increased environmental stress and ecological damage to the sea of which the local population is not yet cognizant of. ተጨማሪ ፎቶ ለማየት

በሀዋሳ ከተማ በበጀት ዓመቱ ከ6 ሺህ በላይ ባለቤት አልባ ውሾች ተወግደዋል

Image
ሀዋሳ፣ ሀምሌ 27፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) በተጠናቀቀው በጀት አመት ከ6 ሺህ በላይ ባለቤት የሌላቸው ውሾች መወገዳቸውን የሀዋሳ ከተማ ጤና መምሪያ ፅፈት ቤት ገለፀ። ውሾቹ ባለቤት አልባና በእብድ ውሻ በሽታ ተጠቂ በመሆናቸው ምክንያት በሽታው በሰዎችም ላይ እየተስፋፋ የመጣበት ሁኔታ በመኖሩ ተወግደዋል ብሏል ፅፈት ቤቱ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት። ከዚህ ባሻገርም በከተማዋ የሚገኙ ባለቤት ያሏቸው ውሾችን የእብድ ውሻ በሽታ መከላከያ ክትባት መሰጠቱን ነው ያስታወቀው። በእብድ ውሻ የተነከሱ ሰዎችም በ48 ስአት ውስጥ ወደ ህክምና ተቋማት ከመጡ በሽታው የመዳን እድሉ ሰፊ በመሆኑ በከተማዋ የሚገኙ የጤና ተቋማት አገልገሎቱን እየሰጡ እንደሚገኙ ኤልሳቤጥ ካሳ ዘግባለች ።

የሲዳማ ዞን ካቢኔዎች የክልል ጥያቄውን ውድቅ ኣደረጉ፤ሲዳማ ለጊዜው ክልል ኣያስፈልገውም ኣሉ

ከሃያ ኣንዱም የዞኑ ወረዳዎች እና ከከተማ ኣስተዳደሮች የመጡት እነዚሁ ካቢኔዎች በወቅቱ የሲዳማ ዞን ኣንገብጋብቢ ኣጀንዳ በሆነው የሲዳማ ክልል ጥያቄ በተመለከተ ተወያይተዋል። በውይይቱም ላይ ስለ ክልል ኣስፈላጊነት እና ካቢኔዎቹ ጥያቄውን በተመለከተ በግል በያዙት ኣቋም ላይ ሂስ እና ግሌ ሂስ ኣካህደዋል። በግምገማው ላይ የዞኑ ካቢኔዎች የሃሳብ መለያየት የታየባቸው ሲሆን፤የክልል ጥያቄውን የምደግፉት የካቢኔ ኣባላት ኣብላጫውን ቁጥር ይዘው ነበር ተብሏል። መድረኩን ይመሩ የነበሩት ካላ ሽፈራው ሽጉጤ  ጽኑ ጸረ ሲዳማ ክልል ኣቋም ያንጸባረቁ ሲሆን፤ የክልል ጥያቄ የመላው የሲዳማ  ህዝብ ጥያቄ ሳይሆን ከኣገሪ ውጭ የሚኖሩት የጥቂት ግለሰቦች ጥያቄ ነው በማለት ኣጣጥለዋል። ከሂስ እና ከግሌ ሂስ ባኃላ ብዙዎቹ ሃሳባቸውን የቀየሩ ሲሆን፤ ሲዳማ ክልል ለጊዜው ኣያስፈልገውም በማለት ኣቋም ይዘዋል። የኣጠቃላይ የግምገማውን ሁኔታ በተመለከተ የውስጥ ኣዋቂ ምንጮች ለወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ እንደተናገሩት፤ በግምገማው ወቅት የካቢኔ ኣባላቱ  የሲዳማን ክልል ጥያቄ እንዳይደግፉ በ ካላ ሽፈራው ሽጉጤ  ከፍተኛ ግፊት ተደርጎባቸዋል። ኣስተያየታቸውን የሰጡት ኣንዳንድ የሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች፤ የዞኑ ካቢኔዎች የሲዳማ ህዝብ ኢኮኖሚያዊ፧ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮቹን እንዲያስፈጽሙለት የመረጣቸው የገዛ ልጆቹ እስከመሆናቸው ድረስ የህዝቡን ጥያቄ በኣግባቡ የመመለስ ግደታ እያለባቸው ለምን የክልል ጥያቄ ወደጎን ልገፉት እንደወደዱ ጠይቀዋል። ይህ በእንዲህ እያለ፤ ከሁለት ሳምንት በፊት ሃዋሳ ዙሪያ ከምገኙት ማልጋ እና ወንዶ ገነት ወረዳዎች ውስጥ ተከስቶ የነበረውን ግጭት ተከትሎ ህዝቡ የክልል ጥያቄ እንዲያነሳ የማሳመን ስራ ሰርታችሃል በሚል