Posts

በ2005 ለሚካሄደው የአካባቢ ምርጫ ለምርጫ አስፈፃሚዎች ስልጠና እየሰጠ ነው

Image
የኢትዮጵያ የምርጫ ህግ በአለም አቀፍ ደረጃ የተቀመጡ መሰረታዊ የምርጫ መርሆዎችን ያካተተ መሆኑ ተገለፀ፡፡ ይህንን ህግ የምርጫ አስፈፃሚዎች ለ2005 በሚካሄደው የአካባቢ ምርጫ ገለልተኛ ሆነው በብቃት ለመተግበር እንዲችሉ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡ የደባሱ ባይለየኝን ዘገባ ከቀጣዩ ቪዲዮ ይመልከቱ፡፡ ዝርዝር ዜናው እዚህ ተጭነው ይመልከቱ

የሀዋሳ ከነማ ስፖርት ክለብ ታሪክ

Image
አመሠራረት የ የሁለት ጊዜ የኢትዮጲያ ፕርሚየር ሊግ አሸናፊ ሀዋሳ ከነማ ስፖርት ክለብ ከኢትዮጲያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ 273 ኪ . ሜ ዕርቀት እና በ 162.804 ሄክታር ቋዳ ስፋት ላይ በምትገኘው ሀዋሳ ከተማ ይገኛል፡፡ የሀዋሳ ከተማ በ 1953 ዓ . ም የተመሰረተች ሲሆን ከ 1985 ዓ . ም ጀምሮ ደግሞ የደቡብ ክልል ርዕሰ ከተማ በመሆን በማገልገል ላይ ትገኛለች፡፡ የደቡብ ክልል አምብርት በሆነችው ሀዋሳ ከተማ የሚገኘው የሀዋሳ ከነማ ስፖርት ክለብ የተመሰረተው በ 1976 ዓ . ም ነው፡፡ የሀዋሳ ከተማ ባለፈው መንግስት ዘመን በሁለት ከፍተኞች የተከፈለች ከተማ ነበረች፡፡ በሁለቱ ከፍተኞች ስም የተቋቋሙ ሁለት ቡድኖችም ነበሩ፡፡ እነዚህ ቡድኖች ከ 1968-1975 ዓ . ም ከቆዩ በሆላ በ 1976 ዓ . ም ሁለቱ ቡድኖች ተዋህደው ሀዋሳ ከነማ ሊወለድ እንደቻለ ከክለቡ ፅ / ቤት ካገኘነው መረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የሀዋሳ ከነማ ክለብ በሀዋሳ ከተማ የከተማውን ነዋሪ የሚወክል አንድ ቡድን መኖር አለበት በሚል በመዘጋጃ ቤቱ ሃላፊዎች ተነሳሽነትና በነዋሪው ጠያቂነት ሊቋቋም እንደቻለ ታውቋል፡፡ ክለቡ በተጠቀሰው ጊዜ ሲመሰረት ሀዋሳ ሐይቅ በሆላም ቀይ ኮከብ የሚባል ስያሜ እንደነበረው የክለቡ ታሪክ ማህደር ያስረዳል፡፡ የሀዋሳ ከነማ ስፖርት ክለብን ከ 1976 ዓ . ም ጀምሮ በባለቤትነት እያስተዳደረ የሚገኘው የሀዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ነው፡፡ ይሁንና ስፖርት ክለቡ በሂደት ራሱን ችሎ መውጣት አለበት በሚል ህሳቤ ከ 1996 ዓ . ም ጀምሮ አሁን ያለውን አደረጃጀት እንዲይዝ ተደርጓል፡፡ ሙሉ ታሪኩን እዚህ ተጭነው ያንቡ

ሃዋሳ የቱሪስት ከተማ ልትመሰርት ነው

Image
አዲስ አበባ፣ ሀምሌ 24፣ 2004 (ኤፍ ቢ ሲ) ሃዋሳ ሌላ የቱሪስት ከተማ ለመመስረት በዝግጅት ላይ ትገኛለች። ከተማው የሃዋሳ ሃይቅን ተሻግሮ በሚገኝ ባዶ ቦታ ላይ ነው የሚመሰረተው። በዚህ ከተማ ላይ ለቱሪስት ምቹ የሆኑ ደረጃቸውን የጠበቁ የመዝናኛ ሎጆችና ሪዞርቶች እንደሚገነቡ ነው የከተማዋ ከንቲባ አቶ ዮናስ ዮሴፍ የተናገሩት። የቱሪስት ከተማው ሃዋሳን መርጠው ለመመልከት የሚመጡ የውጭና የሃገር ውስጥ ጉብኝዎችን ቁጥር በተገቢው ሁኔታ ለማስተናገድ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥርም አመልክተዋል ። የሚመሰረተውን ከተማና ነባሩን ከተማ ለማገናኘት የሚያስችል የትራንስፖርት ስርዓትም እንደሚዘረጋ ተመልክቷል ። እንደ ባልደረባችን  ታደሰ ብዙዓለም ዘገባ የቱሪስት  ከተማዋን ምስረታ  ለመጀመር የሚያስችል ጥናት  ተጠናቆ  ትግበራን  እየተጠባበቀ ይገኛል  ። http://www.fanabc.com/Story.aspx?ID=25131&K=

በሲዳማ ባህል አዳራሽ የተሰበሰቡ ሰዎች አቶ ሽፈራው ሽጉጤን ተቃወሙ

Image
ሲዳማን በተመለከተ ኢሳት ያቀረበውን ዜና(የመጨረሻ ዜና) እዚህ ላይ ይመልከቱ  ሐምሌ ፳፭ (ሀያ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም   ኢሳት ዜና:- የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት በጥንቃቄ የመረጣቸው የሲዳማ ተወላጆች በዛሬው እለት በሲዳማ ባህል አዳራሽ ተሰብስበው የክልሉ መንግስት ያቀረባቸውን ጥያቄዎች ህዝቡ እንዲጠይቅ አደርገዋል። 12 ጥያቄዎች ለባለስልጣናት የቀረቡ ሲሆን፣ አቶ ሽፈራው ” የሲዳማን ጥያቄ አሁን ለማቅረብ እንደማይቻል፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተሽሎአቸው ወደ ስራ ሲመለሱ እንደሚያቀርቡት ተናግረዋል። በከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ በተካሄደው በዚህ ስብሰባ ላይ፣ የስብሰባውን አካሄድ ለመቃወም የሞከሩም ነበሩ። አዋጅ አዋጅ የሚል ርእስ አለው ወረቀት ዛሬ በአዋሳ ሲበተን እንደነበር ዘጋቢያችን ገልጧል። ዛሬ በተበተነው  ወረቀት ላይ ” ጊዜው ወደ መጨረሻው በመቃረቡ ይህንን ትውልድ ገዳይና ዘር ጨራሽ አፈናና እጅ አዙር አገዛዝ ሁከት በሌለበት በሰለጠነ መንገድ አንድ ላይ በመሆን ” እንቃወመው የሚል መልክት ተላልፎአል። ኢሳት ባለፈው ሳምንት ዛሬ በሲዳማ በሀል አዳራሽ ስብሰባ እንደሚካሄድ ዘግቦ እንደነበር ይታወሳል።

Starbucks still uses wrong name for Sidama Coffee

Image
Limited Release of Starbucks Reserve Organic Ethiopia Sidamo® Coffee at Select Retail Locations WHAT:  Starbucks announces the release of Organic Ethiopia Sidamo® coffee, one of the most renowned coffees in the world for its distinctive lemon flavors. For the first time in the Starbucks coffee line, follow the journey from crop to cup by scanning the QR code on the bag. From being meticulously tended by coffee farmers in their family gardens, to how each cherry is ripened and handpicked at the peak of its flavor, to the exquisite flavor notes in each cup, this digital journey is a unique opportunity for customers to learn more about this coffee. Available for a limited time at select stores featuring the Starbucks Reserve™ coffee line, Starbucks will offer Organic Ethiopia Sidamo® in half pound whole bean coffee to make at home for $15 /U.S. and $17/CAN, or to enjoy in-store by the cup through the Clover® brewing system, a tall (12 fl. oz.) cup of brewed coffee starts at $2