Posts

Following intensive malaria prevention and control measures underaken by woreda health offices, the number of new malaria cases reported in the past week has declined in some areas, like Wondo Genet town, Dalla, Aleta Chuko and Dara woredas of Sidama zone

Image
J uly 23, 2012 Agriculture Update Scaling up humanitarian response in key sectors that support food security, including agriculture, remains the priority for both Government and partners in view of the deteriorating food and nutritional security conditions in areas where production has been negatively affected by poor belg (mid-February to May) rains. With the window for planting of long-cycle meher crops (i.e. cereals such as teff, barley, maize, and wheat) now closed in most areas, the focus is on procuring and distributing pulse seeds (i.e. lentils, soy beans, chick peas, haricot beans) to affected farmers. Pulse seeds can still be planted in September in most areas. In pocket areas where meher planting is still viable, long-cycle seed distribution should also be pursued. At present, SNNPR seems to be well covered with various seed and root and tuber crop projects ongoing. The priority areas for expanded agricultural interventions are Amhara and Oromia and, to a lesser extent,

በመልጋ ወረዳ በተነሳ ግጭት ከ19 በላይ ፖሊሶች በጽኑ ቆሰሉ

Image
ሐምሌ ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በትናንትናው እለት ከአዋሳ ከተማ  በ26 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘዋ ማልጋ ወረዳ  በተፈጠረው ግጭት 3 የፌደራል ፖሊስ አባላት በጽኑ መቁሰላቸውን የዘገብን ቢሆንም፣ ዛሬ ዘጋቢያችን ተዘዋውሮ ያጠናከረው መረጃ እንደሚያመለክተው ከ19 በላይ ፖሊሶች እና ከ20 በላይ ነዋሪዎች በጽኑ ቆስለዋል። አናታቸው የተፈነከተ ፣ እግራቸው የተሰበረ፣ እንዲሁም በጥይት የቆሰሉ የፌደራል ፖሊስ አባላት መንገድ ላይ ወድቀው ይታዩ ነበር። በገበያ ላይ የነበረው የአካባቢው ህዝብ ባገኘው መሳሪያ ሁሉ በመጠቀም ከፖሊሶች ጋር ግብ ግብ የገጠመ ሲሆን፣ መሳሪያ የታጠቁ ነዋሪዎች፣ አፈሙዛቸውን ወደ ፖሊሶች በማዞር በርካቶችን አቁስለዋል። ከተለያዩ የዞኑ አካባቢዎች የተውጣጡ የፌደራል ፖሊስ አባላት ወደ አካባቢው ደርሰው በህዝቡ ላይ በከፈቱት ተኩስ ከ20 በላይ ነዋሪዎች በጽኑ ቆስለዋል። የፌደራል ፖሊስ አባላት ግጭቱን ለማብረድ የቻሉት ከአጎራባች ወረዳዎች የፌደራል ፖሊስ አባላትን በብዛት በማምጣት ነው። ፖሊሶቹ ዛሬ በእየቤቱ አሰሳ በማድረግ አንዳንድ ወጣቶችን እየያዙ ወደ እስር ቤት ወስደዋል። በአካባቢው ያለው ውጥረት እየጨመረ፣ የአካባቢው ሰውም ራሱን ከጥቃት ለመከላከል የሚችለበትን መሳሪያ ሁሉ ማዘጋጀቱን ነው የአካባቢው ነዋሪዎች የሚናገሩት። የሲዳማ ተወላጆች ካለፈው ወር ጀምሮ መብታችን ይከበር፣ የክልል አስተዳዳር ይሰጠን የሚሉ ጥያቄዎችን በማቅረብ ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር ሲወዛገቡ እንደነበር ይታወቃል። የመልጋ ወረዳ ነዋሪዎች ያቀረብነው ጥያቄ በአግባቡ እስካልተመለሰ ድረስ፣ መንግስት አለ ብለን ግብር ለመክፈል እንቸገራለን በማለታቸው ነው የትናንትው ግጭት የተነሳው። የአካባቢው ነዋሪዎች ለ

የኦሮሚያ ህዝብ ለሲዳማ ህዝብ ያለውን ኣጋሪነት ኣሳየ፤ በማልጋ ወረዳ በመንግስት ሃይል እና በወረዳው ነዋሪዎች መካከል ተከስቶ በነበረው ግጭት ከሲዳማ ህዝብ ጎን በመቆም ድጋፋን ገለጸ

ከትናንትና ወዲያ በማልጋ ወረዳ ከሲዳማ የክልል ጥያቄ ጋር በተያያዘ በተነሱ ጉዳዩች ላይ ሲመክር የነበረውን የወረዳውን ህዝብ ስብሰባ ለመበተን በሞከሩ የመንግስት ልዩ ሃይል እና በስብሰባው ተሳታፊዎች መካከል ተከስቶ በነበረው ግጭት የኦሮሞ ተወላጆ ከሲዳማ ጎን በመቆም የልዩ ሃይሉን ድርጊት ተቃውመዋል። የወራንቻ ኢንፎ ርሜሽን ኔትዎርክ ከኣካባቢው የሚወጡትን ዜናዎችን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ የኣጎራባች የኦሮሚያ ክልል ነዋሪዎች እና ሲዳማ ለብዙ ዘመናት ኣብረው የኖሩ፤ተጋብተው  የተዋለዱ ወንድማማች ህዝቦች በመሆናቸው ኣንዱ ህዝብ ሲበደል ሌላው ቆሞ ኣያይም። ለዚህም የኦሮሞ ህዝብ የሲዳማ ህዝብ ላነሳው የክልል ይገባኛል ጥያቄ ከመንግስት በኩል እየተሰጠው ያለው ኣሉታዊ ምላሽ ትክክለኛ ባለመሆኑ ከሲዳማ ህዝብ ጎን በመቆም ኣጋሪነቱን በመግለጽ ላይ መሆኑ ተነግሯል። በጉጉማው ግጭት ሰው መሞቱን የተነገረ፤ ሲሆን ዘጠኝ የፈዴራል ፖሊስ እና ሶስት የወረዳው ነዋሪዎች መቁሰላቸው ተገልጿል።

የመልጋ ወረዳ ህዝብ ከ ፌደራል ፖሊስ አባላት ጋር ሲጋጭ ዋለ

ሐምሌ ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ከአዋሳ ከተማ  በ26 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘዋ ማልጋ ወረዳ ዛሬ በተፈጠረው ግጭት 3 የፌደራል ፖሊስ አባላት በጽኑ ሲቆስሉ ከህዝቡም በተመሳሳይ ሰዎች ቆስለዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች ለእረፍት ወደ አካባቢው ከሄዱ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጋር በመሆን፣ በቅርቡ በሲዳማ ዞን የተከሰተውን ችግር እየተወያዩ በነበረት ጊዜ የፌደራል ፖሊስ አባላት  ለመበትን ጥረት በማድረጋቸው ግጭቱ መከሰቱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጠዋል ” በግጭቱ እስካሁን በፖሊስና በህዝብ ወገን ሶስት ሶስት ሰዎች ሲቆስሉ፣ ሁለት መኪኖች ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ ሆነዋል:: ውጅግራ በሚባለው የወረዳው ከተማ 7 ሰዎች መታሰራቸውን፣ የፌደራል ፖሊስ አባላት በብዛት መሰፈራቸው ታውቋል። ከታሰሩት መካከል ታምሩ በሻጋ፣ ሲናራ ሲዳሞ፣ አየለ፣ ዘለላምእንዲሁም  ደረጃ ናስሩ የሚባሉት ይገኙበታል። በአሁኑ ጊዜ አካባቢው በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንደሚገኝ የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ። ስቱዲዮ ከገባን በሁዋላ ሁለት ሰዎች መሞታቸውን መረጃዎች የደረሱን ሲሆን፣ ዘጋቢዎቻችን እስካሁን ለማረጋገጥ አልቻሉም። ቦርቻ፣ ጭኮ እና ሌሎች አካባቢዎችም ከፍተኛ ውጥረት ይታያል። ህዝቡ ከዚህ በፊት እንደነበረው ዝም ብለን አንሞትም በማለት ባገኘው መሳሪያ ሁሉ ለመከላከል መቁረጡን ነው የአካባቢው ነዋሪዎች የሚናገሩት። በሲዳማ ዞን ከክልል እና ከመብት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ካለፈው ወር ጀምሮ ተደጋጋሚ ግጭት ሲከሰት  መቆየቱን መዘገባችን ይታወሳል።

ሰበር ዜና ፦ በሲዳማ ዞን በማልጋ ወረዳ በመንግስታ ሃይሎች እና በሰላማዊ ሰዎች መካከል በተከሰው ግጭት ሰዎች መሞታቸው እና መቁሰላቸው ተነገረ

በዛሬው እለት በማልጋ ወረዳ በጉጉማ ከተማ የሲዳማ ህዝብ ለክልሉ መንግስት ለቀረበው የክልል ጥያቄዎች የመንግስት ኣካል የሰጠውን ኣሉታዎ ምላሽ በመቃዎም ተቃውሞኣቸውን በገለጹ ሰላማዊ ሰዎች እና በመንግስት ልዩ ሃይል መካከል ግጭት ተከስቷል። ያልተረጋገጡ ከኣካባቢው የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፤ ወደ ማታ ኣካባቢ በተከሰተው በዚህ ግጭት ሁለት ሰዎች ሞተዋል እና ሁለት ሰዎች ደግሞ በጹኑ ቆስለዋል። ግጭቱን ተከትሎ ኣካባቢው በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ያለ ሲሆን፤ በመሆኑ በርካታ ቁጥር ያለው የመንግስት ልዩ ሃይል ወደ ኣካባቢው በመግባት ላይ መሆኑን የኣይን እማኞች ለወራንቻ ኢንፎ ርሜሽን ኔትዎርክ ገልጸዋል። ሞቱና ቆሰሉ ስለተባሉ ሰዎች ቁጥር እና ማንነት በተመለከተ እንዲሁም  ስለ መረጃው ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ወደ ኣካባቢው በስልክ ያደረግ ነው መኩራ  በኔዎርክ መጨናነቅ ምክንያት ኣልተሳከም። ሆኖም በጉዳዩ ላይ ማረጋገጫ እና ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን ለኣንባቢዎቻችን እናሳውቃለን።