Posts

ሲዳማ ቡና አሰልጣኙን ዳኜን አሰናብቷ በቦታው ሌላ ሰው ሊቀጥር ነው የሀዋሳ ከነማው ዘላለም ሊገባ ነው ተብሎ እየተጠበቀ ነው

ማክሰኞ ሐምሌ 3 ቀን 2004 ዓ.ም ፀጋዬ ኪዳነማሪያም የሐረር ቢራ አሰልጣኝ ቡና ገብቷል ፣ዛሬ ሲዳማ ቡና አሰልጣኙን ዳኜን አሰናብቷ በቦታው ሌላ ሰው ሊቀጥር ነው የሀዋሳ ከነማው ዘላለም ሊገባ ነው ተብሎ እየተጠበቀ ነው፣ ባንኮች ጥላሁንን አሰናብቶ ውበቱ አባተን በሀላፊነት መድቧል፣ የሲዳማ ቡናው ግብ ጠበቂ ሲሳይ ባንጫ 550ሺ ብር ተከፍሎት ደደቢት ፈርሟል፣ መሱድ መሐመድ ሌላ ክለብ 650ሺ ብር ቀርቦለታል ዛሬ ከቡና ጋር ተነጋግሯል ከጠየቀው ክለብ የቀረበለትን ገንዘብ ሰምተዋል ቡና ምን ያህል ሊከፍለው እንደሚፈልግ ማወቅ ይፈልጋል ድርድር ላይ ናቸው ፡፡ ይህን ያህል ክፈሉኝ አላለም፡፡ ከሌላ ክለብ የቀረበለትን ስለሰሙ የነሱን ዋጋ ማወቅ ይፈልጋል፡፡ የክለቡን መልስ ይጠበቃል፡፡ ቡና መሱድ፣ዳዊት ( ሞገስና እስጢፋኖስ) መዳኔ፣ሙሉዓለም ኮንትራታቸው አልቋል፡፡ የወቅቱን ገበያ አይተው ክለቡ ሊደራደር ይገባል፡፡ ጊዮርጊስ አዳነ እና ያሬድ ኮንትራታቸው አልቋል፡፡ ለዘንድሮ 1 ሚሊየን ነው የተጠየቀው፡፡ በድርድር እስከ 700ሺ ይፈረማል ነው የተባለው፡፡ ተጫዋቹ በእግር ኳሱ ለውጥ ማምጣቱ አለማምጣቱ ሳይሆን ዛሬ በፊርማ መልክ ለነገ መተዳደሪያቸው ለመስጠት የተሸለ ነው የሚሆነው፡፡ በሌላ በኩል በሴቶች በኩል የፊርማ ክፍያ እየተለመደ መጥቷል በጣም ጥሩ ጅማሬ ነው፡፡ በሴቶቹ የፊርማ የተጀመረው የዛሬ ሶስት አመት አካባቢ ነው፡፡ በ2002 ሰሚራ 3ሺ አገኘች፡፡ ባለፋው ዓመት ብርቱካን ወደ ደዲቢት ስትገባ 35ሺ በማግኘት ሪከርድ ሰበረች፡፡ አሁን ደግሞ ዳጋማዊት ወደ ባንክ በ50ሺ ብር ለመዘዋወር ስምምነት ላይ ደርሳለች፡፡ ዳጋማዊት የብሔራዊ ቡድን ተጠባባቁ በረኛ ነች፡፡\ http://librogk.com/2010-08-10-08-41-47.html

HwU’s department of Informatics in collaboration with Google

Image
HwU’s department of Informatics in collaboration with  G o o g l e  Company has started capacity building project on computer technology for teachers and students selected from governmental and non-governmental schools around Hawassa. Mr.Tesfaye Baye, lecturer at informatics department and the project coordinator noted that the main objective of the training is enhancing teachers’ and students’ computer skills at the lower level mainly at high& preparatory schools there by making them beneficiaries of modern computer technologies. In the training, that lasts for a year (2012/13 academic year), it is intended to involve more than 500 teachers and students. On top of that, it was noted Google Company has donated 10,000 US dollars to successfully run the project. It was also noted that the university has won this project of Google Company competing with other strong East African Universities.   http://www.hu.edu.et/hu/index.php/84-hawassa-university/events/news/197-hwus

4187 Students graduated from Hawassa University

Image
On the graduation ceremony held for two days, convocation for the main campus graduate and for Agricultural and Medicine College together held on July 14 and15/2012 respectively. Dr. Yoseph Mamo president of Hawassa University noted that of the total graduates, 488 were masters’ degree holders and 83 were doctorate degree holders. He also underscored the immense progress in increasing the number and level of academic programs in the university. He said the number of academic programs which were 8 at the beginning of the establishment, now multiplied incredibly, i.e. 64 1 st  degree programs, 43 2 nd  degree programs and 4 PhD programs. Honorary guest of the occasion Mr. Shiferaw Shigute, President of the Southern Nations, Nationalities, and People's Region on his part emphasized how hard the government is working in getting access of tertiary education to the majority of the people. He said the number of higher institutions which were 4 and 5 in number fifteen

የቡና ኤክስፖርት እንቅፋት ገጥሞታል

የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ኢንተርፕራይዝ በሚያካሂደው የመልቲ ሞዳል አሠራር ምክንያት በተፈጠረው ችግር፣ ባለፉት ሁለት ሳምንት ቡና ወደ ውጭ መላክ እንዳላስቻለ ምንጮች ገለጹ፡፡ በ2004 ዓ.ም ዓመት በቡና ንግድ ላይ የተፈጠረው ችግር በአዲሱ በጀት ዓመትም ሊደገም ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል፡፡   የመልቲ ሞዳል አሠራርን ተግባራዊ ያደረገው ኢንተርፕራይዝ ወደ አገር ውስጥ በሚገቡ ምርቶች ላይ ብቻ ሳይሆን፣ ወደ ውጭ በሚላኩ ምርቶች ላይም መስተጓጎል እየተፈጠረ መሆኑን እየተናገረ ነው፡፡   በ2003 ዓ.ም. ወደ ውጭ የተላከው የቡና መጠን 197 ሺሕ ቶን ነው፡፡ በ2004 ዓ.ም. በአገሪቱ ከፍተኛ የቡና ምርት ቢኖርም ከታቀደው 270 ሺሕ ቶን ውስጥ የተላከው 170 ሺሕ ቶን ብቻ ነው፡፡   ይህ ሊሆን የቻለው ንግድ ሚኒስቴር በበጀት ዓመቱ በተለያዩ ጊዜያት የቡና ንግድን በሚመላከት ባወጣቸው መመርያዎች ምክንያት ነው ሲሉ፣ የቡና ነጋዴዎች ጣታቸውን በሚኒስቴሩ ላይ ይቀስራሉ፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ የቡና ነጋዴዎች በውጭ ደንበኞቻቸው ዕምነት እየታጠባቸው መሆኑን እየገለጹ ነው፡፡   “ውል በገባነው መሠረት ቡና ማቅረብ ተስኖን ዓመቱን አጠናቀናል፤” ሲሉ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የቡና ኤክስፖርተር ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡   የተፈጠሩት ችግሮች የኢትዮጵያ ቡና በዓለም አቀፍ ደረጃ በጥራቱና በጣዕሙ ቢታወቅም፣ በዋጋ ከሁሉም አገር ቡናዎች የመጨረሻ ደረጃ ላይ እንዲገኝ አድርጎታል፡፡   ችግሮቹን ከፈጠሩት መካከል ቡና በኮንቴይነር ይላክ መባሉና በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል የሚወጣው ጨረታ የፈጠረው የአላላክ ዘዴ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት የቡና ላኪዎች ማኅበርና ታዋቂ የቡና ላኪዎች ከንግድ ሚኒስቴር ጋር በ

ከሃዋሳ ወጥቶ የነበረው የፈዴራል ሃይል ተመልሶ ገባ፤ከየወረዳዎች የተወጣጡ የኣገር ሽማግሌዎች የክልል ጥያቄን በተመለከተ ከዞኑ ኣስተዳዳሪ ጋር ያደረጉት ውይይት ያለ ውጤት ተጠናቀቀ ቀጣይ ውይይት በሚቀጥለው ሳምንት ለማደረግ ታቅዷል

Image
ካለፈው ወር ጅምሮ የሲዳማ የክልል ጥያቄ በተመለከተ የተቀጣጠለውን  ህዝባዊ ንቅናቄን ለመቆጣጠር የሃዋሳን ከተማ ጨምሮ በኣንዳንድ የሲዳማ ወረዳዎች ሰፍሮ የነበረው የፊዴራል ሃይል ባለፉት ሳምንታት መውጣቱ የሚታወስ ሲሆን ለጊዜው ባልታወቀ ምክንያት በዚህ ሳምንት ውስጥ ወደ ሲዳማ  ተመልሷል። የፈዴራል ሃይሉ ወደ ሲዳማ መመለስን በተመለከተ የተለያዩ ኣስተያየቶች እየተሰጡ ሲሆን ህዝባዊ ንቅናቄው  በተለይ በወረዳዎች ተቀጣጥሎ  በመቀጠሉ ለሃይሉ መመለስ ምክንያት ሳይሆን ኣይቀርም ተብሏል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከዞኑ ወረዳዎች የተወጣጡ ሽማግሌዎችን ያካተተ ኣንድ የሲዳማ ልኡካን ቡድን በትናንትናው እለት ከዞኑ ኣመራር ጋር የክልል ጥያቄን በተመለከተ የተወያይ ሲሆን ስብሳባው ያለ በቂ ውጤት ተጠናቋል። የሲዳማ  ሽማግሌዎች ህገ መንግስቱ በምፈቅደው መሰረት የክልል ጥያቄ በሲዳማ ዞን ምክር ቤት ኣባለት እንዲቀርብ ጥያቄ  ያቀረቡ ሲሆን፤ በካላ ሚሊዮን ማትዎስ የተመራው የዞን ካቢኔ የሽማግሌዎቹን ጥያቄ ሳይቀበል ቀርቷል። ካላ ሚሊዮን በስብሰባው ላይ የክልል ጥያቄ ከዚህ በፊት ተነስቶ የነበረ ነገር ግን በልማት ጥያቄ የተተካ በመሆኑ መልሶ ማንሳት ኣያስፈልግ የምል ኣቋም ኣንጸባርቀዋል። በመረጧቸው እና በገዛ ልጆቻቸው ምላሽ ያልተደሰቱት ሽማግሌዎቹ የስልጣን እርከኑን ተከትለው ከላይ ካሉት ባለስልጣናት ጋር  ለመነጋገር ለሚቀጥለው ሳምንት ቀጠሮ ይዘው ተለያይተዋል።