Posts

በሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር ውስጥ በርካታ የኣመራር የስራ መደቦች ላላፉት ሰባት እና ስምንት ወራት ክፍት ሆነው መቆየታቸው በከተማዋ ለሚካሄዱት ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ስራዎች ማነቆ መሆናቸውን ኣንዳንድ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ፤የኣመራር ስራ መደቦችቹ ለረዥም ጊዜያት ክፍት ሆነው መቆየታቸው መንግስት የከተማዋን ኣስተዳደር ከሲዳማ ለመንጠቅ ከሚያደርገው እንቅስቃሴ ጋር ሳይያያዝ ኣቀርም የሚል ጥርጣሬ ፈጥሯል

ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ ነዋሪዎችና ሰራተኞች ለወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ እንደተናገሩት፤ የከተማው ኣስተዳደር ምክትል ከንትባና ንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ የስራ መደብን ጨምሮ በማዘጋጃ እና በስምንቱም ክፍለ ከተማዎች ቢያንስ ኣራት ኣራት የኣመራር የስራ መደቦች ላላፉት ሰባት እና ስምንት ወራት ሰው ኣልተመደበባቸውም። የእነዚህ  መደቦች የእለትተእለት ስራዎች በተወከሉ ሰዎች በመከሄድ ላይ ያሉ ሲሆን፤ ሰው ካልተመደበባቸው መደቦች መካከል የከተማዋ የመንግስት ኮሚኒኬሽን፤ የማዘጋጃ ቤቱ ምክትል ኣስተዳዳር መደብ፤ ግቢይትና ህብረት ስራ መምሪያ እና የፍትህ መምሪያ ይገኙበታል። በየስራ መደቦቹ ላይ ከዚህ በፊት ተመድበው ይሰሩ የነበሩ ግለሰቦች በተለያዩ ምክንያቶች ስራ የለቀቁ ወይም እንዲለቁ የተደረጉ መሆኑ ሲገለጽ፤ መደቦቹ ለረዥም ጊዚያት ክፍት መሆናቸው በከተማዋ ለሚካሄዱ የልማት ስራዎች ኣፈጻጸም ላይ ችግር መፈጠራቸው ተገልጿል። እንደኣንዳንድ የከተማዋ ነዋሪዎች ኣስተያየት ከሆነ መንግስት የከተማዋን ኣስተዳደር ከሲዳማ እጅ ለማውጣት ከተማዋን ያስተዳድሩ በነበሩ የብሄሩ ተወላጆች ላይ የተለዩ ስነ ምግባራቸውን የሚያወርዱ ገጽታዎችን እየቀባ ያለ ምንም ተጨባጭ  ሲያስር ቆይቷል። ይህ ኣይነቱ የመንግስት ድርጊት የሲዳማ ኣመራሮች የማስተዳደር ኣቅም የላቸውም፤ በክራይ ስብሳብነት የተዘፈቁ ናቸው የምል ግንዛቤ በከተማው ነዋሪ ዘንድ ለማስያዝና ኣመራሩን በሌላ ኣመራር ለመተካት የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኝ ለማድረግ የታለመ  ሳይሆን ኣይቀርም ተብለዋል። ለዚህም ማሳያነት በቁልፍ የኣመራር መደቦች ላይ ከነበሩ ግለሰቦች መካከል መሬት በመቸብቸብ እና በሌሎች ወንጀሎች ተወንጅለው ላለፉት ሰባት እና ስምንት ወራት ታስረው

ማኑ ጎባስራ ሻራማ

Image
ከሬሆ ማንቶ ዛላቃሽ ኣዲንታን ካሬሆ ይኖሞ ሲዳሙ ቆቆው ሃዋሲ ሲዳሙ ቆቆዎ እካታ ማይራላ ዎሎቱ ሂናሱ ዳንቺሌ ቁቱዋ ሄሬና ኮባላ ዛላቁራ ባሲ ዲጮማኖ ቅሽሪሮ ዋሲ ዲኖሴ ጎሎንሁ ዳላሲ ያናቴ ቃኤክራ ቃፊ ሳትላፌ ሳትላፌ። ዳጉራው ዳጉራው ሲዴ ሎጶ ያን ጋራማዎ ሻራማዎ ... annitine maccishe

ሲዳማ ሱስተናንሴ(Sidama Sustenance) የተባለ በሲዳማ ለምግብነት በጥቅም ላይ በሚውለው በዌሴ ላይ የተጻፈ ኣዲስ መጽህፍ ገበያ ላይ ዋለ።

Image
በዶና ሲያን የተጻፈ ይህንን መጽህፍ በሲዳማና ሲዳማን በተመለከቱ ጉዳዮች ትንተና ይጀምር እና ስለ ዌሴ ተክል ሳይንሳዊ ኣመጣጥ ይተርካል፤ ከዛም ስለ ዌሴ ኣተካከል ከችግኝ ማለትም ከፉንታ ኣቆራረጥ እስከ ኣፋፋቅ ያትታል። በመጨረሻም ከዌሴ ምርቶች የተለያዩ የምግብ ኣይነቶች ኣዘገጃጀት ላይ ስፊ ማብራሪያ  ይሰጣል። መጽሀፉ እያንዳንዱን ማብራሪያ በፎቶ  ኣስደግፎ የሚስጥ ሲሆ ን ኣቀራረቡ ማንም ሰው በሚረዳ መልኩ ነው። በመጽሀፉ ውስጥ ካሉ ፎቶዎች መካከል የምከተሉት ይገኛሉ፦  ይህንን የሲዳማን ባህላዊ ምግብ ለኣለም የሚያስተዋውቀውን መጽሀፍ ገዝታችሁ ለማንበብ ኣቅም የለንም ወይም ልናገኘው ኣልቻልንም የምትሉ ካላችሁ በሚቀጥለው ሊንክ ሙሉ መጽሀፉን ኦንላይን ማንበብ ትችላላችሁ። መልካም ንባብ  Sidama Sustenance

የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ከ190 በላይ የምርምር ስራዎችን በማካሄድ ላይ ይገኛል

Image
አዋሳ ሃምሌ 10/2004 የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል የሚያስችሉ ከ190 በላይ የተለያዩ የምርምር ሰራዎችን በማካሄድ ላይ እንደሚገኝ የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት አስታወቁ ። ከነዚህም ውስጥ 90 በመቶ ያህሉ በዩኒቨርስቲው አካባቢ በሚገኙ የቴክኖሎጂ ማመንጫና ማስፋፊያ ወረዳዎች ላይ መሆኑም ተገልጧል ። የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ እንደገለጹት ዩኒቨርስቲው በነደፈዉ የአምስት ዓመት የምርምርና የልማት ስትራቴጂ ለአርሶ አደሩ ከፍተኛ ጠቀሜታ በሚያስገኙና ችግር ፈቺ ለሆኑ ምርምሮች ቅድሚያ ትኩረት ሰጥቷል ። ዩኒቨርሲቲዉ በተለይ በምግብና በቢራ ገብስ ቴክኖሎጂ፣ በጤፍ አመራረት፣ በድንች ፣ በደጋና በወይና ደጋ የቅባት እህሎች፣ በምርጥ የቡና ዝርያ ብዜት፣ እንዲሁም በእንሰት አዘገጃጀት ቴክኖሎጂ ላይ በስፋት እየሰራ መሆኑን አስታዉቀዋል ። በእንስሳት እርባታና በተፈጥሮ ሃብት ልማት ዘርፍ ከክልሉ ግብርና ቢሮ ጋር በመተባበር ምርታማ የሆኑ የእንስሳት መኖ ዝርያዎችን በምርምር ጣቢያዎች በማባዛት የማስተዋወቅ፣ የተሻሻሉ የበግና የፍየል ዝርያዎችን የማዳቀል፣ ዘመናዊ የንብ ማነብ ቴክኖሎጂዎችን የማስተዋወቅ ስራ እያካሄደ መሆኑን ገልጠዋል ። ዉጤታማነታቸዉ በምርምር የተረጋገጡ የሳርና የዛፍ ዝርያዎችን የተፋሰስ ስራዎች በተካሄዱባቸዉ አካባቢዎች እንዲተከሉ ለአርሶ አደሮች በማከፋፈል አበረታች ተግባር እያከናወነ መሆኑን ዶክተር ዮሴፍ አስታዉቀዋል ። በተጨማሪ ዩኒቨርሰቲው የአምስት ዓመቱን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ስኬታማ ለማድረግ ስድስት የቴክኖሎጂ መንደሮችን በመለየት ከክልሉ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮና ከሌሎች የባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በማምረት፣ በማስተዋወቅና በማስፋፋት ላይ እንደ

በሀዋሳ ከተማ ከ40ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራም ተጀመረ፡፡

Image
ሃዋሳ ሃምሌ 9/2004 በሀዋሳ ከተማ ከ40ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራም ዛሬ ተጀመረ፡፡ የወጣቶችን የስራ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት እንዲጠናከር ሁሉም ባለድርሻ አካላት የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የከተማው አስተዳደር ከንቲባ ጥሪ አቀረቡ፡፡ የፕሮግራሙ መጀመር ምክንያት በማድረግ በሀዋሳ መስቀል አደባባይ ዛሬ በተዘጋጀው የትውውቅ ስብሰባና የቸግኝ ተከላ ስነ ስርዓት ላይ የከተማው ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወጣት መልካሙ ጋጋዶ እንደገለጸው የከተማው ወጣቶች ባለፉት ሶስት ዓመታት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተደራጀ መንገድ ተሳታፊና ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊ ወጣቶቹ ጉልበታቸውን፣ እውቀታቸውንና ገንዘባቸውን ለአካባቢው ልማትና ደህንነት በነፃ ያበረከቱበት በሂደትም ሌሎችን በመርዳት ከማህበረሰቡ የተለያየ እውቀት የቀስሙበት የተግባር መሳሪያ ነው ብሏል፡፡ በዘንድሮም ክረምት ከከተማው የተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ከወጣት አደረጃጀቶች ጋር በመተባበር እራሳቸውንና ህብረተሰቡን ጠቅመው የከተማውን ልማት በሚያፋጥኑ የበጎ አድራጎት ተግባራት ለመሰማራት እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ወጣት መልካሙ አብራርቷል ። የከተማው አስተዳደር ህፃናት፣ ሴቶችና ወጣቶች ፣ መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ ስምረት ግርማ በበኩላቸው የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ በከተማው ከተጀመረ ወዲህ የወጣቶች ተነሳሽነትና ፍላጎት እየጨመረ መጥቷል ብለዋል፡፡ በ2002 የክረምት ወራት በስድስት ዓይነት የበጎ ፈቃድ አገልገሎት መስኮች 9ሺህ 463 ወጣቶች ተሳታፊ የነበሩበት ሲሆን በቀጣይ አመት የስራ መስኮቹ ወደ ስምንት የተሳታፊ ወጣቶች ቁጥር ደግሞ ከ36 ሺህ በላይ በማሳደግ በርካታ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል፡፡ በ