Posts

በሀዋሳ ከተማ ከ40ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራም ተጀመረ፡፡

Image
ሃዋሳ ሃምሌ 9/2004 በሀዋሳ ከተማ ከ40ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራም ዛሬ ተጀመረ፡፡ የወጣቶችን የስራ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት እንዲጠናከር ሁሉም ባለድርሻ አካላት የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የከተማው አስተዳደር ከንቲባ ጥሪ አቀረቡ፡፡ የፕሮግራሙ መጀመር ምክንያት በማድረግ በሀዋሳ መስቀል አደባባይ ዛሬ በተዘጋጀው የትውውቅ ስብሰባና የቸግኝ ተከላ ስነ ስርዓት ላይ የከተማው ወጣቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ወጣት መልካሙ ጋጋዶ እንደገለጸው የከተማው ወጣቶች ባለፉት ሶስት ዓመታት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተደራጀ መንገድ ተሳታፊና ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳታፊ ወጣቶቹ ጉልበታቸውን፣ እውቀታቸውንና ገንዘባቸውን ለአካባቢው ልማትና ደህንነት በነፃ ያበረከቱበት በሂደትም ሌሎችን በመርዳት ከማህበረሰቡ የተለያየ እውቀት የቀስሙበት የተግባር መሳሪያ ነው ብሏል፡፡ በዘንድሮም ክረምት ከከተማው የተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ከወጣት አደረጃጀቶች ጋር በመተባበር እራሳቸውንና ህብረተሰቡን ጠቅመው የከተማውን ልማት በሚያፋጥኑ የበጎ አድራጎት ተግባራት ለመሰማራት እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ወጣት መልካሙ አብራርቷል ። የከተማው አስተዳደር ህፃናት፣ ሴቶችና ወጣቶች ፣ መምሪያ ሃላፊ ወይዘሮ ስምረት ግርማ በበኩላቸው የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ በከተማው ከተጀመረ ወዲህ የወጣቶች ተነሳሽነትና ፍላጎት እየጨመረ መጥቷል ብለዋል፡፡ በ2002 የክረምት ወራት በስድስት ዓይነት የበጎ ፈቃድ አገልገሎት መስኮች 9ሺህ 463 ወጣቶች ተሳታፊ የነበሩበት ሲሆን በቀጣይ አመት የስራ መስኮቹ ወደ ስምንት የተሳታፊ ወጣቶች ቁጥር ደግሞ ከ36 ሺህ በላይ በማሳደግ በርካታ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን አስረድተዋል፡፡ በ

ጡማኖና ፋቂሳ ስለተባሉ የሲዳማ ነገድ ኣባቶች እና መካነ መቃብሮቻቸው ምን ያህል ያውቃሉ?

Image
  ቴላሞ የጡማኖ  መታሰቢያ የጡማኖ መካነ መቃብር እና የሃገር ሽማግሌው አቶ ሲዳሞ ቢረጋ ከለኩ ከተማ በስምንት ኪሎ ሜትር ገደማ ርቀት ላይ የሚገኘው ቴላሞ ነው፤ ቴላሞ የሲዳማ አድባር ነው ሲሉ የሃገር ሽማግሌዎቹ ይገልጻሉ፡፡ አረንጓዴ ምድር ምን ማለት እንደሆነ በቴላሞ ቅጥር ግቢ ያሉት ሃገር በቀል ግዙፍ የዛፍ ዝርያዎች ለትውልድ የቆሙ ማስረጃዎች ናቸው፡፡ መልከአ-ምድራዊ ውበቱ ይማርካል፤ ከደኑ መሃል በአጥር የተከበበ አንድ ቅጥር አለ፤ በዚህ ቅጥር ውስጥ የሲዳማ ነገድ አባት የሆነው የጡማኖ መቃብር ይገኛል፡፡ በስፍራው በየእጽዋቱ ስር የአረብኛ ጽሁፍ ያለባቸው ድንጋዮች ይገኛሉ፤ እንደ አካባቢው ሽማግሌዎች ገለጻ እነዚህ የአረብኛ ጽሁፍ ያለባቸው ድንጋዮች መቃብሮች ናቸው፡፡ ሲዳሞ ቢራጋ የሃገር ሽማግሌ ናቸው፤ በየግዜው ለተለያየ ጉዳይ ወደ ቴላሞ ይመጣሉ፤ ይህንን ስናጠናቅር በስፍራው ያገኘናቸውም ለተመሳሳይ ዓላማ በቴላሞ ውብ ቅጥር ግቢ ለውይይት አረፍ እንዳሉ ነው፡፡ የሲዳማ የሃገር ሽማግሌዎች የሚለብሱትን ባህላዊ አለባበስ የለበሱት አቶ ሲዳሞ ቢራጋ ስፍራውን በሚመለከት አንዳንድ ጥያቄዎችን ስናቀርብላቸው በማራኪ አተራረክ ለዛ መልሰውልናል…መነሻችን ደግሞ ቴላሞ ምንድን ነው የሚል ነበር አቶ ሲዳሞ በተረጋጋ ሁኔታ ረጃጅም የቅጥሩ ዛፎች ላይ አይናቸውን ተክለው አብራሩልን….   ይሄ ቦታ ቴላሞ ይባላል፤ ጡማኖ የሲዳማ አባት ነው፤ እዚህ ነው የተቀበረው፤ ቦታው ብዙ ዓመቱ ነው….ማን ይቆጥረዋል ብዙ ነው፤ እዚህ የወለደ ሰው አሁን አስራ ስድስት ትውልድ ሆኗል፡፡ የቅጥሩን ዙሪያ ገባ በዓይናቸው ቃኘት አድርገው መልሰው ወደ ሽማግሌዎቹ በመመልከት የቴላሞን አካባቢ ሁለንተናዊ እሴት በወፍ በረር መተረኩን ቀጥለዋል….. በዓመት በዓመት ኮርማ ይገባል…

AGRICULTURAL COOPERATIVES AND RURAL LIVELIHOODS: EVIDENCE FROM ETHIOPIA(SIDAMA)

ABSTRACT:  Agricultural cooperatives are important rural organizations supporting livelihood development and poverty reduction. In recognition of such roles of cooperatives, Ethiopia showed a renewed interest in recent years in promoting cooperative sector development. However, there is lack of a wider and systematic analysis to produce sufficient empirical evidence on the livelihood development and poverty reduction impacts of cooperatives in the country. Using a matching technique on rural household income, saving, agricultural input expenditure and asset accumulation as indicator variables, this paper evaluates the livelihood impact of agricultural cooperatives in Sidama zone, Ethiopia. The finding shows that cooperatives improved the livelihoods of service user farmers through impacting better income, more savings and reduced input costs. In view of such evidence, further promotion, deepening and supporting of agricultural cooperatives is recommended. Source:http://onlineli

The program shows the tensions boiled over at an east Melbourne hotel as Oromian, Ogadenian, Sidama and Ethiopian nationals protested against the presence of the TPLF’s delegates in Australia.

Image
The program shows the tensions boiled over at an east Melbourne hotel as Oromian, Ogadenian, Sidama and Ethiopian nationals protested against the presence of the TPLF’s delegates in Australia. http://gadaa.com/oduu/14799/2012/07/15/abo-dhimmaa-guddaa/

የተባበሩት የሲዳማ ፓርቲዎች ለነጻነትና ለፍትህ ዋና ጸሀፊ የሆኑት አቶ ደንቦባ ናቲ በሲዳማ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ከኢሳት ጋር ያደረጉት የስልክ ቃለ ምልልስ

Image
 ከካላ ደንቦባ ናቲ ጋር የተደረገውን ውይይት ከ6:17 ደቂቃ ጀምረው መከታተል ይችላሉ። ኢሳት ዜና:-በቅርቡ ከሲዳማ ዞን እጣ ፈንታ እንዲሁም አጠቃላይ የፍትህ ጥያቄ ጋር በተያያዘ በአካባቢው የተነሳው ውጥረት መቀጠሉን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመለከተ ባለፈው ሳምንት የግንቦት7 አባላት ናቸው ተብለው የተረጠረጠሩ በርካታ ወጣቶች መያዛቸውን የደቡብ ክልል ዘጋቢያችን የገለጠ ሲሆን፣ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት የሆኑት አቶ በረከትንና አቶ አባይ ጸሀየን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ፓርቲዎች በችግሩ ዙሪያ በአዋሳ ከተማ ውይይት እያደረጉ ነው። የተባበሩት የሲዳማ ፓርቲዎች ለነጻነትና ለፍትህ ዋና ጸሀፊ የሆኑት አቶ ደንቦባ ናቲ ለኢሳት እንደተናገሩት የሲዳማ ሽማግሌዎችና የአካባቢው ሰዎች በጉዳዩ ዙሪያ ውይይት እያደረጉ ሲሆን ተቃውሞው እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል:: አቶ ደንቦባ እንዳሉት የሲዳማ የኢህአዴግ አባላት በብዛት አባልነታቸውን እየሰረዙ ነው::